Biblia Todo Logo
La Biblia Online

- Anuncios -




ሕዝቅኤል 6:7 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

7 ሙታ​ኖ​ቻ​ች​ሁም በመ​ካ​ከ​ላ​ችሁ ይወ​ድ​ቃሉ፤ እኔም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሆንሁ ታው​ቃ​ላ​ችሁ።

Ver Capítulo Copiar

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

7 የታረዱ ሰዎቻችሁ በመካከላችሁ ይወድቃሉ፤ እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

7 የተገደሉትም በመካከላችሁ ይወድቃሉ፥ በዚያን ጊዜ እኔ ጌታ እንደሆንሁ ታውቃላችሁ።

Ver Capítulo Copiar

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

7 የተገደሉት በአካባቢያችሁ ይጣላሉ፤ ከዚያ በኋላ እናንተ እኔ እግዚአብሔር መሆኔን ታውቃላችሁ።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

7 ተወግተውም የሞቱት በመካከላችሁ ይወድቃሉ፥ እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ።

Ver Capítulo Copiar




ሕዝቅኤል 6:7
43 Referencias Cruzadas  

እን​ግ​ዲ​ህም አም​ላ​ካ​ችን አቤቱ፥ የም​ድር መን​ግ​ሥ​ታት ሁሉ አንተ ብቻ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አም​ላክ እንደ ሆንህ ያውቁ ዘንድ ከአ​ሦር ንጉሥ እጅ አድ​ነን።”


ግብ​ፃ​ው​ያ​ንም በፈ​ር​ዖ​ንና በሰ​ረ​ገ​ሎቹ፥ በፈ​ረ​ሰ​ኞ​ቹም ላይ ክብር በአ​ገ​ኘሁ ጊዜ እኔ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሆንሁ ያው​ቃሉ።”


እኔም የፈ​ር​ዖ​ንን ልብ አጸ​ና​ለሁ፤ እር​ሱም ከኋ​ላ​ቸው ይከ​ተ​ላ​ቸ​ዋል፤ እኔም በፈ​ር​ዖ​ንና በሠ​ራ​ዊቱ ሁሉ ላይ እከ​ብ​ራ​ለሁ፤ ግብ​ፃ​ው​ያ​ንም ሁሉ እኔ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሆንሁ ያው​ቃሉ።” እነ​ር​ሱም እን​ዲሁ አደ​ረጉ።


ግብ​ፃ​ው​ያ​ንም እጄን በግ​ብፅ ላይ በዘ​ረ​ጋሁ ጊዜ፥ የእ​ስ​ራ​ኤ​ል​ንም ልጆች ከመ​ካ​ከ​ላ​ቸው በአ​ወ​ጣሁ ጊዜ፥ እኔ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሆንሁ ያው​ቃሉ።”


ወደ ሜዳ ብወጣ፥ እነሆ በሰ​ይፍ የሞቱ አሉ፤ ወደ ከተ​ማም ብገባ፥ እነሆ በራብ የከሱ አሉ፤ ነቢ​ዩና ካህኑ ወደ​ማ​ያ​ው​ቋት ሀገር ሄደ​ዋ​ልና።”


ስለ​ዚህ ልጆ​ቻ​ቸ​ውን ለራብ ስጥ፤ ለሰ​ይ​ፍም እጅ አሳ​ል​ፈህ ስጣ​ቸው፤ ሚስ​ቶ​ቻ​ቸ​ውም የወ​ላድ መካ​ንና መበ​ለ​ቶች ይሁኑ፤ ወን​ዶ​ቻ​ቸ​ውም በሞት ይጥፉ፤ ጐል​ማ​ሶ​ቻ​ቸ​ውም በጦ​ር​ነት ጊዜ በሰ​ይፍ ይመቱ።


በዚ​ያም ቀን የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ግዳ​ዮች ከም​ድር ዳር ጀምሮ እስከ ምድር ዳር ድረስ ይሆ​ናሉ፤ አይ​ለ​ቀ​ስ​ላ​ቸ​ውም፤ በም​ድር ላይ እንደ ጕድፍ ይሆ​ናሉ እንጂ አይ​ሰ​በ​ሰ​ቡም፤ አይ​ቀ​በ​ሩ​ምም።


ጤት። በሰ​ይፍ የሞ​ቱት በራብ ከሞ​ቱት ይሻ​ላሉ፤ እነ​ዚህ የም​ድ​ርን ፍሬ አጥ​ተው ተወ​ግ​ተ​ውም ዐል​ፈ​ዋል።


በሰ​ይፍ ትወ​ድ​ቃ​ላ​ችሁ፤ በእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ተራ​ሮች እፈ​ር​ድ​ባ​ች​ኋ​ለሁ፤ እኔም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሆንሁ ታው​ቃ​ላ​ችሁ።


በት​እ​ዛዜ አል​ሄ​ዳ​ች​ሁ​ምና፥ ፍር​ዴ​ንም አላ​ደ​ረ​ጋ​ች​ሁ​ምና፥ በዙ​ሪ​ያ​ች​ሁም እን​ደ​ሚ​ኖ​ሩት እንደ አሕ​ዛብ ሕግ አድ​ር​ጋ​ች​ኋል።”


በአ​ሕ​ዛ​ብም መካ​ከል በም​በ​ት​ና​ቸው ጊዜ፥ በሀ​ገ​ሮ​ችም በም​ዘ​ራ​ቸው ጊዜ፥ እኔ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሆንሁ ያው​ቃሉ።


ለም​ድ​ሪ​ቱም ሕዝብ፦ ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ስለ​ሚ​ኖሩ ስለ እስ​ራ​ኤል ምድ​ርም እን​ዲህ ይላል፦ የሚ​ኖ​ሩ​ባት ሁሉ በዐ​መፅ ይኖ​ራ​ሉና ምድ​ሪቱ በመ​ላዋ ትጠፋ ዘንድ እን​ጀ​ራ​ቸ​ውን በች​ግር ይበ​ላሉ፤ ውኃ​ቸ​ው​ንም በድ​ን​ጋጤ ይጠ​ጣሉ።


ያለ ገለባ የመ​ረ​ጋ​ች​ሁ​ት​ንም ቅጥር አፈ​ር​ሳ​ለሁ፤ ይወ​ድ​ቃል፤ ወደ ምድ​ርም እጥ​ለ​ዋ​ለሁ፤ መሠ​ረ​ቱም ይታ​ያል፤ እር​ሱም ይና​ዳል፤ በመ​ካ​ከ​ሉም ትጠ​ፋ​ላ​ችሁ፤ እኔም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሆንሁ ታው​ቃ​ላ​ችሁ።


ሽፋ​ኖ​ቻ​ች​ሁን ደግሞ እቀ​ድ​ዳ​ለሁ፤ ሕዝ​ቤ​ንም ከእ​ጃ​ችሁ አድ​ና​ለሁ፤ ከዚ​ያም ወዲያ በእ​ጃ​ችሁ ለመ​ታ​ደን አይ​ሆ​ኑም፤ እኔም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሆንሁ ታው​ቃ​ላ​ችሁ።


ስለ​ዚህ፥ ሐሰ​ትን አታ​ዩም፤ እን​ግ​ዲ​ህም ከንቱ ምዋ​ር​ትን አታ​ም​ዋ​ር​ቱም፤ ሕዝ​ቤ​ንም ከእ​ጃ​ችሁ አድ​ና​ለሁ፤ እኔም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሆንሁ ታው​ቃ​ላ​ችሁ።”


እጄም ሐሰ​ተኛ ራእ​ይን በሚ​ያዩ፥ ሕዝ​ቤ​ንም ለማ​ታ​ለል በከ​ንቱ በሚ​ያ​ም​ዋ​ርቱ ነቢ​ያት ላይ ትሆ​ና​ለች። እነ​ር​ሱም በሕ​ዝቤ ማኅ​በር ውስጥ አይ​ኖ​ሩም፤ በእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ቤት መጽ​ሐፍ አይ​ጻ​ፉም፥ ወደ እስ​ራ​ኤ​ልም ምድር አይ​ገ​ቡም፤ እኔም ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሆንሁ ያው​ቃሉ።


ፊቴ​ንም በዚያ ሰው ላይ አደ​ር​ጋ​ለሁ፤ እን​ዲ​ጠ​ፋም አደ​ር​ገ​ዋ​ለሁ፤ ከሕ​ዝ​ቤም መካ​ከል አስ​ወ​ግ​ደ​ዋ​ለሁ፤ እኔም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሆንሁ ታው​ቃ​ላ​ችሁ።


ፊቴ​ንም በእ​ነ​ርሱ ላይ አጸ​ና​ለሁ፤ ከእ​ሳ​ትም አይ​ወ​ጡም፤ እሳ​ትም ይበ​ላ​ቸ​ዋል፤ ፊቴ​ንም በእ​ነ​ርሱ ላይ በአ​ጸ​ናሁ ጊዜ እኔ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሆንሁ ታው​ቃ​ላ​ችሁ።


እኔም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሆንሁ እን​ዲ​ያ​ውቁ አጠ​ፋ​ቸው ዘንድ ማኅ​ፀን የሚ​ከ​ፍ​ተ​ውን ሁሉ በአ​መ​ጡ​ልኝ ጊዜ፥ በመ​ባ​ቸው አረ​ከ​ስ​ኋ​ቸው።


ከእ​ና​ን​ተም ዘንድ ዐመ​ፀ​ኞ​ች​ንና የበ​ደ​ሉ​ኝን እለ​ያ​ለሁ፤ ከኖ​ሩ​ባ​ትም ምድር አወ​ጣ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ ወደ እስ​ራ​ኤል ምድር ግን አይ​ገ​ቡም፤ እኔም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሆንሁ ታው​ቃ​ላ​ችሁ።


ለአ​ባ​ቶ​ቻ​ች​ሁም እሰ​ጣት ዘንድ እጄን ወደ አነ​ሣ​ሁ​ላ​ቸው ምድር ወደ እስ​ራ​ኤል ሀገር ባገ​ባ​ኋ​ችሁ ጊዜ፥ እኔ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሆንሁ ታው​ቃ​ላ​ችሁ።


የእ​ስ​ራ​ኤል ቤት ሆይ! እንደ ክፉ መን​ገ​ዳ​ች​ሁና እንደ ርኩስ ሥራ​ችሁ ሳይ​ሆን ስለ ስሜ ስል በሠ​ራ​ሁ​ላ​ችሁ ጊዜ፥ እኔ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሆንሁ ታው​ቃ​ላ​ችሁ፥” ይላል ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር።


በአ​ሕ​ዛ​ብም ፊት ከአ​ንቺ እወ​ር​ሳ​ለሁ፤ እኔም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሆንሁ ያው​ቃሉ።”


እን​ግ​ዲህ በደ​ላ​ችሁ በላ​ያ​ችሁ ላይ ይመ​ለ​ሳል፤ እና​ን​ተም የጣ​ዖ​ቶ​ቻ​ች​ሁን ኀጢ​አት ትሸ​ከ​ማ​ላ​ችሁ፤ እኔም ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሆንሁ ታው​ቃ​ላ​ችሁ።”


ሕዝ​ቅ​ኤ​ልም ምል​ክት ይሆ​ና​ች​ኋል፤ እርሱ እንደ አደ​ረገ ሁሉ እና​ንተ ታደ​ር​ጋ​ላ​ችሁ፤ ይህም በመጣ ጊዜ እኔ ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሆንሁ ታው​ቃ​ላ​ችሁ።


በዚያ ቀን አፍህ ላመ​ለ​ጠው ይከ​ፈ​ታል፤ አን​ተም ትና​ገ​ራ​ለህ፤ ከዚ​ያም ወዲያ ዲዳ አት​ሆ​ንም፤ ምል​ክ​ትም ትሆ​ና​ቸ​ዋ​ለህ፤ እኔም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሆንሁ ያው​ቃሉ።”


በመ​ዓት መቅ​ሠ​ፍ​ትም ታላቅ በቀል አደ​ር​ግ​ባ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ በቀ​ሌ​ንም በላ​ያ​ቸው በአ​ደ​ረ​ግሁ ጊዜ፥ እኔ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሆንሁ ያው​ቃሉ።”


በሜዳ ያሉ​ትም ሴቶች ልጆ​ችዋ በሰ​ይፍ ይገ​ደ​ላሉ፤ እኔም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሆንሁ ያው​ቃሉ።


ቸነ​ፈ​ር​ንም በአ​ንቺ ላይ፥ ደም​ንም በጎ​ዳ​ናሽ ላይ እሰ​ድ​ዳ​ለሁ፤ ከዙ​ሪ​ያ​ሽም በላ​ይሽ ባለ ሰይፍ የተ​ወጉ በመ​ካ​ከ​ልሽ ይወ​ድ​ቃሉ፤ እኔም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሆንሁ ያው​ቃሉ።


ግብ​ፃ​ው​ያ​ን​ንም በአ​ሕ​ዛብ መካ​ከል እበ​ት​ና​ለሁ፤ በሀ​ገ​ሮ​ችም መካ​ከል እዘ​ራ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ ሁሉም እኔ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሆንሁ ያው​ቃሉ።”


የግ​ብ​ፅ​ንም ምድር ባድ​ማና ውድማ በአ​ደ​ረ​ግሁ ጊዜ፥ ምድ​ርም በመ​ላዋ በጠ​ፋች ጊዜ፥ የሚ​ኖ​ሩ​ባ​ት​ንም ሁሉ በቀ​ሠ​ፍሁ ጊዜ፥ እኔ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሆንሁ ያው​ቃሉ።


የእ​ስ​ራ​ኤል ቤት ርስት ባድማ ስለ ሆነ በላዩ ደስ እን​ዳ​ለህ፥ እን​ዲሁ አደ​ር​ግ​ብ​ሃ​ለሁ፤ የሴ​ይር ተራራ ሆይ! አን​ተና መላው ኤዶ​ም​ያስ ባድማ ትሆ​ና​ላ​ችሁ፤ እኔም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሆንሁ ታው​ቃ​ለህ።”


ታላቅ እሆ​ና​ለሁ፤ እቀ​ደ​ስ​ማ​ለሁ፤ እመ​ሰ​ገ​ና​ለ​ሁም፤ በብዙ አሕ​ዛ​ብም ዐይን የታ​ወ​ቅሁ እሆ​ና​ለሁ፤ እኔም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሆንሁ ያው​ቃሉ።


ሬሳ​ዎ​ቻ​ቸው በጣ​ዖ​ቶ​ቻ​ቸው መካ​ከ​ልና በመ​ሠ​ዊ​ያ​ዎ​ቻ​ቸው ዙሪያ በወ​ደቁ ጊዜ በረ​ዣ​ዥም ኮረ​ብታ ሁሉ፥ በተ​ራ​ሮ​ችም ራሶች ሁሉ፥ በዕ​ን​ጨ​ቱም ጥላ ሥር ለጣ​ዖ​ቶ​ቻ​ቸው ሁሉ፥ መል​ካም መዓ​ዛን ባጠ​ኑ​በት ከቅ​ጠሉ ሁሉ በታች ሬሳ​ዎ​ቻ​ቸው በወ​ደቁ ጊዜ እኔ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሆንሁ ያው​ቃሉ።


በም​ት​ኖ​ሩ​ባ​ትም ስፍራ ሁሉ ከተ​ሞች ይፈ​ር​ሳሉ፥ የኮ​ረ​ብታ መስ​ገ​ጃ​ዎ​ችም ሁሉ ውድማ ይሆ​ናሉ፤ መሠ​ዊ​ያ​ዎ​ቻ​ች​ሁም ይፈ​ር​ሳሉ፤ ባድ​ማም ይሆ​ናሉ፤ ጣዖ​ቶ​ቻ​ች​ሁም ይሰ​በ​ራሉ፤ ያል​ቃ​ሉም፤ የፀ​ሐይ ምስ​ሎ​ቻ​ች​ሁም ይጠ​ፋሉ፤ ሥራ​ች​ሁም ይሻ​ራል።


“ነገር ግን በሀ​ገ​ሮች በተ​በ​ተ​ና​ችሁ ጊዜ ከእ​ና​ንተ ከአ​ሕ​ዛብ ጦር የዳ​ኑ​ትን አስ​ቀ​ራ​ለሁ።


ዐይ​ኔም አይ​ራ​ራ​ል​ሽም፤ እኔም ይቅር አል​ል​ሽም፤ መን​ገ​ድ​ሽ​ንም አመ​ጣ​ብ​ሻ​ለሁ፤ ርኵ​ሰ​ት​ሽም በመ​ካ​ከ​ልሽ ነው፤ እኔም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሆንሁ ታው​ቃ​ላ​ችሁ።”


ዐይ​ኔም አይ​ራ​ራም፤ እኔም ይቅር አል​ልም፤ መን​ገ​ድ​ሽ​ንም አመ​ጣ​ብ​ሻ​ለሁ፤ ርኵ​ሰ​ት​ሽም በመ​ካ​ከ​ልሽ ነው፤ እኔም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የም​ቀ​ሥፍ እንደ ሆንሁ ታው​ቃ​ላ​ችሁ።


እር​ሱም፥ “ቤቱን አር​ክሱ፤ ወጥ​ታ​ችሁ ግደሉ፤ በሙ​ታ​ንም መን​ገ​ዶ​ችን ሙሉ” አላ​ቸው።


Síguenos en:

Anuncios


Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos