Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -




ዘፀአት 21:6 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

6 ጌታው ወደ ቤተ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፈራ​ጆች ይው​ሰ​ደው፤ ወደ ደጁም፥ ወደ መቃ​ኑም አቅ​ርቦ አፍ​ን​ጫ​ውን በወ​ስፌ ይብ​ሳው፤ ለዘ​ለ​ዓ​ለ​ምም ባሪ​ያው ይሁ​ነው።

Ver Capítulo Copiar

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

6 ጌታው ወደ ዳኞች ይውሰደው፤ ወደ በር ወይም ወደ በሩ መቃን ወስዶ ጆሮውን በወስፌ ይብሳው፤ ከዚያም ዕድሜ ዘመኑን የርሱ አገልጋይ ይሆናል።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

6 ጌታው ወደ እግዚአብሔር ያቅርበው፥ ወደ በሩ ወይም ወደ መቃኑ አቅርቦ ጆሮውን በወስፌ ይብሳው፤ ለዘለዓለምም ያገልግለው።

Ver Capítulo Copiar

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

6 ጌታው የእግዚአብሔር አገልጋዮች ወደ ሆኑ ፈራጆች ዘንድ ይውሰደው፤ እዚያም ከበር ወይም ከበር መቃን አጠገብ አቁሞ ጆሮውን በወስፌ ይብሳው፤ ከዚያም በኋላ እስከ ዕድሜ ልኩ ድረስ ባርያ ሆኖ ያገልግለው።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

6 ወደ ደጁም ወደ መቃኑ አቅርቦ ጆሮውን በወስፌ ይብሳው፤ ለዘላለምም ባሪያው ይሁን።

Ver Capítulo Copiar




ዘፀአት 21:6
24 Referencias Cruzadas  

እነ​ር​ሱም፥ “ለዚህ ሕዝብ አሁን አገ​ል​ጋይ ብት​ሆን፥ ብት​ገ​ዛ​ላ​ቸ​ውም፥ መል​ሰ​ህም በገ​ር​ነት ብት​ነ​ግ​ራ​ቸው፥ በዘ​መኑ ሁሉ አገ​ል​ጋ​ዮ​ችህ ይሆ​ኑ​ል​ሃል” ብለው ተና​ገ​ሩት።


አቤቱ፥ እንደ አንተ ማን ነው? አቤቱ፥ ዝም አት​በል፥ ቸልም አት​በል።


እኔም በዚ​ያች ሌሊት በግ​ብፅ ሀገር አል​ፋ​ለሁ፤ በግ​ብ​ፅም ሀገር ከሰው እስከ እን​ስሳ ድረስ በኵ​ርን ሁሉ እገ​ድ​ላ​ለሁ፤ በግ​ብ​ፅም አማ​ል​ክት ሁሉ ላይ በቀ​ልን አደ​ር​ግ​ባ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ እኔ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ነኝ።


“ሁለት ሰዎች እርስ በር​ሳ​ቸው ቢጣሉ፥ ያረ​ገ​ዘ​ች​ንም ሴት ቢያ​ቈ​ስሉ ተሥ​ዕ​ሎተ መል​ክእ ያል​ተ​ፈ​ጸ​መ​ለት ፅን​ስም ቢያ​ስ​ወ​ር​ዳት፥ የሴ​ቲቱ ባል የጣ​ለ​በ​ትን ያህል ካሳ ይክ​ፈል፤


ባሪ​ያ​ውም፦ ጌታ​ዬን፥ ሚስ​ቴን፥ ልጆ​ች​ንም እወ​ድ​ዳ​ለሁ፤ አር​ነ​ትም አል​ወ​ጣም ብሎ ቢና​ገር፥


“ሴት ልጁን ለባ​ር​ነት አሳ​ልፎ የሰጠ ቢኖር ሴቶች ባሪ​ያ​ዎች አር​ነት እን​ደ​ሚ​ወጡ እር​ስዋ ትውጣ።


“ፈራ​ጆ​ችን አት​ስ​ደብ፥ የሕ​ዝ​ብ​ህ​ንም አለቃ ክፉ አት​ና​ገ​ረው።


ፈራ​ጆ​ች​ሽ​ንም እንደ ቀድሞ፥ አማ​ካ​ሪ​ዎ​ች​ሽ​ንም እንደ መጀ​መ​ሪያ ጊዜ አስ​ነ​ሣ​ለሁ፤ ከዚ​ያም በኋላ የጽ​ድቅ ከተማ፥ የታ​መ​ነ​ችም ጽዮን ርእሰ ከተማ ተብ​ለሽ ትጠ​ሪ​ያ​ለሽ።


“ምድ​ርም ለእኔ ናትና፥ እና​ን​ተም በእኔ ፊት እን​ግ​ዶ​ችና መጻ​ተ​ኞች ናች​ሁና ምድ​ርን ለዘ​ለ​ዓ​ለም አት​ሽጡ።


እንደ ምን​ደ​ኛና እንደ ስደ​ተኛ ከአ​ንተ ጋር ይሁን፤ እስከ ኢዮ​ቤ​ልዩ ዓመ​ትም ያገ​ል​ግ​ልህ።


በውስጥዋ ያሉ አለቆችዋ እንደሚያገሡ አንበሶች ናቸው፣ ፈራጆችዋም እስከ ነገ ድረስ ምንም እንደማያስቀሩ እንደ ማታ ተኵላዎች ናቸው።


በዚ​ያን ጊዜ ፈራ​ጆ​ቻ​ች​ሁን አዘ​ዝ​ኋ​ቸው። አል​ኋ​ቸ​ውም፦ የወ​ን​ድ​ሞ​ቻ​ች​ሁን ነገር ስሙ፤ በሰ​ውና በወ​ን​ድሙ፥ ከእ​ር​ሱም ጋር ባለው መጻ​ተኛ መካ​ከል በጽ​ድቅ ፍረዱ።


እርሱ ግን አን​ተ​ንና ቤት​ህን ስለ ወደደ፥ በአ​ን​ተም ዘንድ መኖር መል​ካም ስለ​ሆ​ነ​ለት፦ ‘አል​ወ​ጣም’ ቢል፥


አንተ ወስፌ ወስ​ደህ በቤ​ትህ በር ላይ ጆሮ​ውን ትበ​ሳ​ዋ​ለህ፤ ለዘ​ለ​ዓ​ለ​ምም ባሪያ ይሆ​ን​ል​ሃል። በሴት ባሪ​ያ​ህም ደግሞ እን​ዲሁ ታደ​ር​ጋ​ለህ።


“አም​ላ​ክህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በሚ​ሰ​ጥህ በሀ​ገ​ርህ ደጅ ሁሉ በየ​ነ​ገ​ዶ​ችህ ፈራ​ጆ​ች​ንና መባ​ውን የሚ​ጽ​ፉ​ትን ሹሙ፤ ለሕ​ዝ​ቡም ቅን ፍር​ድን ይፍ​ረዱ።


ሐና ግን ከእ​ርሱ ጋር አል​ወ​ጣ​ችም። ለባ​ል​ዋም፥ “ሕፃ​ኑን ጡት እስከ አስ​ጥ​ለው፥ ከእ​ኔም ጋር እስ​ኪ​ወ​ጣና በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት እስ​ኪ​ታይ ድረስ አል​ወ​ጣም፤ በዚ​ያም ለዘ​ለ​ዓ​ለም ይኖ​ራል” ብላ​ዋ​ለ​ችና።


አን​ኩ​ስም፥ “በሕ​ዝቡ በእ​ስ​ራ​ኤል ዘንድ እጅግ የተ​ጠላ ሆኖ​አል፤ ስለ​ዚ​ህም ለዘ​ለ​ዓ​ለም ባሪያ ይሆ​ነ​ኛል” ብሎ ዳዊ​ትን አመ​ነው።


ዳዊ​ትም አን​ኩ​ስን፥ “አሁን አገ​ል​ጋ​ይህ የሚ​ያ​ደ​ር​ገ​ውን ንገ​ረው” አለው። አን​ኩ​ስም ዳዊ​ትን፥ “እን​ግ​ዲህ በዘ​መኑ ሁሉ ራሴን ጠባቂ አደ​ር​ግ​ሃ​ለሁ” አለው።


Síguenos en:

Anuncios


Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos