Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -




ዘዳግም 30:7 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

7 አም​ላ​ክ​ህም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይህ​ችን መር​ገም ሁሉ በጠ​ላ​ቶ​ች​ህና በሚ​ጠ​ሉህ በሚ​ያ​ሳ​ድ​ዱ​ህም ላይ ያመ​ጣ​ታል።

Ver Capítulo Copiar

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

7 አምላክህ እግዚአብሔር ይህን ርግማን ሁሉ በሚጠሉህና በሚያሳድዱህ ጠላቶችህ ላይ ያደርገዋል።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

7 ጌታ አምላክህም ይህን ርግማን ሁሉ በጠላቶችህና በሚጠሉህ በሚያሳድዱህም ላይ ያደርገዋል።

Ver Capítulo Copiar

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

7 እነዚህንም መርገሞች ሁሉ አንተን በሚጠሉህና በሚጨቊኑህ ጠላቶችህ ላይ ይመልስባቸዋል፤

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

7 አምላክህም እግዚአብሔር ይህችን መርገም ሁሉ በጠላቶችህና በሚጠሉህ በሚያሳድዱህም ላይ ያመጣታል።

Ver Capítulo Copiar




ዘዳግም 30:7
28 Referencias Cruzadas  

አንተ ግን ቃሌን ብት​ሰማ፥ ያል​ሁ​ህ​ንም ሁሉ ብታ​ደ​ርግ፥ ጠላ​ቶ​ች​ህን እጥ​ላ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ የሚ​ቃ​ወ​ሙ​ህ​ንም እቃ​ወ​ማ​ለሁ።


ስለ​ዚህ እን​ዲህ ይሆ​ናል፤ ጌታ ሥራ​ውን ሁሉ በጽ​ዮን ተራ​ራና በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ላይ በፈ​ጸመ ጊዜ የአ​ሦ​ርን ንጉሥ የኵሩ ልብን ፍሬ፥ የዐ​ይ​ኑ​ንም ከፍታ ትም​ክ​ሕት ይቀ​ጣል።


እነሆ ስሜ የተ​ጠ​ራ​ባ​ትን ከተማ አስ​ጨ​ን​ቃት ዘንድ እጀ​ም​ራ​ለሁ፤ በውኑ እና​ንተ መን​ጻ​ትን ትነ​ጻ​ላ​ች​ሁን? በም​ድር በሚ​ኖሩ ሁሉ ላይ ሰይ​ፍን እጠ​ራ​ለ​ሁና አት​ነ​ጹም፥ ይላል የሠ​ራ​ዊት ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር።


ስለ​ዚህ የሚ​በ​ሉህ ሁሉ ይበ​ላሉ፤ የሚ​ማ​ር​ኩ​ህም ሁላ​ቸው ይማ​ረ​ካሉ፤ የዘ​ረ​ፉ​ህም ይዘ​ረ​ፋሉ፤ የሚ​ማ​ር​ኩ​ህ​ንም ሁሉ ለመ​ማ​ረክ አሳ​ልፌ እሰ​ጣ​ለሁ።


ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፦ ኤዶ​ም​ያስ በይ​ሁዳ ቤት ላይ በቀል አድ​ር​ጎ​አ​ልና፥ ቂምም ይዞ​አ​ልና፥ በቀ​ል​ንም ተበ​ቅ​ሎ​አ​ልና፤


ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፥ “ፍል​ስ​ጥ​ኤ​ማ​ው​ያን በቀ​ልን አድ​ር​ገ​ዋ​ልና፥ በቀ​ላ​ቸ​ው​ንም አጽ​ን​ተ​ዋ​ልና፥ እስ​ራ​ኤ​ልም ለዘ​ለ​ዓ​ለም ይጠፉ ዘንድ ነፍ​ሳ​ቸው ደስ ይላ​ታ​ልና፤


ለአ​ሞ​ንም ልጆች እን​ዲህ በል፦ የጌ​ታን የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቃል ስሙ፤ ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፦ መቅ​ደሴ በረ​ከሰ ጊዜ የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ምድር ባድማ በሆ​ነች ጊዜ፥ የይ​ሁ​ዳም ቤት በተ​ማ​ረኩ ጊዜ ስለ እነ​ርሱ ደስ ብሎ​ሃ​ልና፤


ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላ​ልና፦ በእ​ጆ​ችህ አጨ​ብ​ጭ​በ​ሃ​ልና፥ በእ​ግ​ሮ​ች​ህም አሸ​ብ​ሽ​በ​ሃ​ልና፥ ሰው​ነ​ት​ህም በእ​ስ​ራ​ኤል ምድር ላይ ደስ ብሎ​አ​ታ​ልና፤


ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፥ “ሞአ​ብና ሴይር፦ እነሆ የይ​ሁዳ ቤት እንደ አሕ​ዛብ ሁሉ ነው ብለ​ዋ​ልና፤


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፦“ወን​ድ​ሙን በሰ​ይፍ አሳ​ድ​ዶ​ታ​ልና፥ በም​ድር ላይም ማኅ​ፀ​ንን አር​ክ​ሶ​አ​ልና፥ የሚ​ዘ​ል​ፈ​ው​ንና የሚ​ያ​ስ​ደ​ነ​ግ​ጠ​ውን በር​ብ​ሮ​አ​ልና፥ መዓ​ቱ​ንም ለዘ​ለ​ዓ​ለም ጠብ​ቆ​አ​ልና ስለ ሦስት ወይም ስለ አራት የኤ​ዶ​ም​ያስ ኀጢ​አት መቅ​ሠ​ፍ​ቴን ከማ​ድ​ረግ አል​መ​ለ​ስ​ላ​ቸ​ውም።


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፥ “ዳር​ቻ​ቸ​ውን ያሰፉ ዘንድ የገ​ለ​ዓ​ድን ነፍሰ ጡሮች ቀድ​ደ​ዋ​ልና ስለ ሦስት ወይም ስለ አራት የአ​ሞን ልጆች ኀጢ​አት መቅ​ሠ​ፍ​ቴን ከማ​ድ​ረግ አል​መ​ለ​ስም።


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፥ “የገ​ለ​ዓ​ድን ነፍሰ ጡሮች በብ​ረት መጋዝ ሰን​ጥ​ቀ​ዋ​ቸ​ዋ​ልና ስለ ሦስት ወይም ስለ አራት የደ​ማ​ስቆ ኀጢ​አት መቅ​ሠ​ፍ​ቴን ከማ​ድ​ረግ አል​መ​ለ​ስ​ላ​ቸ​ውም።


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፥ “በኤ​ዶ​ም​ያስ ይዘ​ጉ​ባ​ቸው ዘንድ የሰ​ሎ​ሞ​ንን ምርኮ ማር​ከ​ዋ​ልና ስለ ሦስት ወይም ስለ አራት የጋዛ ኀጢ​አት መቅ​ሠ​ፍ​ቴን ከማ​ድ​ረግ አል​መ​ለ​ስ​ላ​ቸ​ውም።


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፥ “የሰ​ሎ​ሞን ምር​ኮ​ኞ​ችን በኤ​ዶ​ም​ያስ ዘግ​ተ​ዋ​ልና፥ የወ​ን​ድ​ሞ​ች​ንም ቃል ኪዳን አላ​ሰ​ቡ​ምና ስለ ሦስት ወይም ስለ አራት የጢ​ሮስ ኀጢ​አት አል​መ​ለ​ስ​ላ​ቸ​ውም።


“በወ​ን​ድ​ምህ በያ​ዕ​ቆብ ላይ ስለ ተደ​ረገ ኀጢ​አ​ትና ግድያ ኀፍ​ረት ይከ​ድ​ን​ሃል፤ ለዘ​ለ​ዓ​ለ​ምም ትጠ​ፋ​ለህ።


በዚያም ቀን ኢየሩሳሌምን ለአሕዛብ ሁሉ ከባድ ድንጋይ አደርጋታለሁ፣ የሚሸከሙአት ሁሉ እጅግ ይቈስላሉ፣ የምድርም አሕዛብ ሁሉ በላይዋ ላይ ይከማቻሉ።


አሁ​ንም፥ እነሆ፥ ወደ ሕዝቤ እሄ​ዳ​ለሁ፤ ና፥ ይህ ሕዝብ በኋ​ለ​ኛው ዘመን በሕ​ዝ​ብህ ላይ የሚ​ያ​ደ​ር​ገ​ውን እነ​ግ​ር​ሃ​ለሁ።”


አር​ፎ​አል፥ እንደ አን​በ​ሳና እንደ አን​በሳ ደቦል ተጋ​ድ​ሞ​አል፤ ማን ያስ​ነ​ሣ​ዋል? የሚ​መ​ር​ቁህ ሁሉ የተ​መ​ረቁ ይሁኑ፤ የሚ​ረ​ግ​ሙ​ህም ሁሉ የተ​ረ​ገሙ ይሁኑ።”


አን​ተም ተመ​ል​ሰህ የአ​ም​ላ​ክ​ህን የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቃል ትሰ​ማ​ለህ፤ ዛሬም እኔ የማ​ዝ​ዝ​ህን ትእ​ዛ​ዙን ሁሉ ታደ​ር​ጋ​ለህ።


በግ​ብ​ፃ​ው​ያን ላይ ሲመጣ ያየ​ኸ​ውን ክፉ ሕማ​ምና ደዌ ሁሉ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ከአ​ንተ ያር​ቅ​ል​ሃል፤ ያየ​ኸ​ው​ንም መከራ ሁሉ ወደ አንተ አያ​መ​ጣ​ውም፤ ከአ​ን​ተም በሚ​ጠ​ሉህ ሁሉ ላይ ይመ​ል​ሰ​ዋል።


Síguenos en:

Anuncios


Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos