Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -




ሐዋርያት ሥራ 27:17 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

17 ከዚህ በኋላ ተጋ​ግ​ዘን በገ​መድ አጠ​ና​ከ​ር​ናት፤ ከዚ​ህም ቀጥሎ ቀዛ​ፊ​ዎች ወደ ጥልቁ ባሕር እን​ዳ​ይ​ወ​ድቁ በፈሩ ጊዜ ሸራ​ውን አወ​ረዱ፤እን​ዲ​ሁም እን​ድ​ን​ሄድ አደ​ረ​ግን።

Ver Capítulo Copiar

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

17 ጀልባዋንም ወደ ላይ ጐትተው ካወጧት በኋላ መርከቧ እንዳትፈራርስ ዙሪያዋን በገመድ ጠምጥመው አሰሯት፤ ስርቲስ ከተባለው አሸዋማ ደለል ጋራ ሄደው እንዳይላተሙ ስለ ፈሩም፣ የመርከቧን ሸራ አውርደው እንዲሁ በዘፈቀደ እንድትነዳ አደረጉ።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

17 ወደ ላይም ካወጡአት በኋላ መርከቡን በገመድ አስታጥቀው አጸኑ፤ ስርቲስም ወደሚሉት ወደ አሸዋ እንዳይወድቁ ፈርተው ሸራውን አውርደው እንዲሁ ተነዱ።

Ver Capítulo Copiar

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

17 መርከበኞቹ ጀልባውን ወደ መርከቡ ስበው ካወጡት በኋላ በመርከቡ ዙሪያ ገመድ ጠመጠሙ፤ መርከቡ ሱርቲስ ወደምትባል አሸዋማ ስፍራ እንዳይወድቅ ፈርተው ሸራውን አወረዱና በነፋስ እየተነዱ ሄዱ።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

17 ወደ ላይም ካወጡአት በኋላ መርከቡን በገመድ አስታጥቀው አጸኑ፤ ስርቲስም ወደሚሉት ወደ አሸዋ እንዳይወድቁ ፈርተው ሸራውን አውርደው እንዲሁ ተነዱ።

Ver Capítulo Copiar




ሐዋርያት ሥራ 27:17
5 Referencias Cruzadas  

ከዚ​ህም በኋላ ቄዳ ወደ​ም​ት​ባል ደሴት እስ​ክ​ን​ገባ ድረስ ነፋሱ ነፈሰ፤ በጭ​ን​ቅም ታን​ኳ​ች​ንን ለመ​ግ​ታት ቻልን።


ነገር ግን ወደ አን​ዲት ደሴት እን​ደ​ር​ሳ​ለን።”


ድን​ጋ​ያማ በሆነ ቦታም እን​ዳ​ይ​ወ​ድቁ ፈሩ፤ ስለ​ዚ​ህም ከመ​ር​ከቡ በስ​ተ​ኋላ አራት መል​ሕቅ በባ​ሕሩ ላይ ጣሉ፤ ፈጥኖ እን​ዲ​ነ​ጋም ጸለዩ።


መል​ሕ​ቁ​ንም ፈት​ተው በባ​ሕር ላይ ጣሉት፤ የሚ​ያ​ቆ​ሙ​በ​ት​ንም አመ​ቻ​ች​ተው እንደ ነፋሱ አነ​ፋ​ፈስ መጠን ትን​ሹን ሸራ ሰቀሉ፤ ወደ ባሕሩ ዳር​ቻም ሄድን።


መር​ከ​ቢ​ቱም በሁ​ለት ታላ​ላቅ ድን​ጋ​ዮች መካ​ከል ተቀ​ረ​ቀ​ረች፤ ባሕ​ሩም ጥልቅ ነበረ። ከወ​ደ​ፊ​ቷም ተያ​ዘች፤ አል​ተ​ን​ቀ​ሳ​ቀ​ሰ​ች​ምም፤ ከሞ​ገ​ዱም የተ​ነሣ በስ​ተ​ኋላ በኩል ጎን​ዋን ተሰ​ብራ ተጐ​ረ​ደች፤ ቀዛ​ፊ​ዎ​ችም ወደ​ፊት ሊገ​ፉ​አት አል​ቻ​ሉም።


Síguenos en:

Anuncios


Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos