Biblia Todo Logo
La Biblia Online

- Anuncios -




2 ዜና መዋዕል 34:31 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

31 ንጉ​ሡም በዐ​ምዱ ቆሞ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ተከ​ትሎ እን​ዲ​ሄድ፥ ትእ​ዛ​ዙ​ንና ምስ​ክ​ሩን፥ ሥር​ዐ​ቱ​ንም በፍ​ጹም ልቡና በፍ​ጹም ነፍሱ እን​ዲ​ጠ​ብቅ፥ በዚ​ህም መጽ​ሐፍ የተ​ጻ​ፈ​ውን የቃል ኪዳን ቃል እን​ዲ​ያ​ደ​ርግ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ቃል ኪዳን አደ​ረገ።

Ver Capítulo Copiar

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

31 ንጉሡም በዐምዱ አጠገብ በእግዚአብሔር ፊት ቆሞ እግዚአብሔርን እንደሚከተል ትእዛዞቹን፣ ደንቦቹን፣ ሥርዐቶቹን በፍጹም ልቡና በፍጹምም ነፍሱ እንደሚጠብቅ፣ በዚህም መጽሐፍ የተጻፈውን ኪዳን እንደሚያጸና በእግዚአብሔር ፊት ኪዳኑን አደሰ።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

31 ንጉሡም በስፍራው ቆሞ ጌታን ተከትሎ እንዲሄድ፥ ትእዛዛቱንና ምስክሩን ሥርዓቱንም በፍጹም ልቡና በፍጹም ነፍሱ እንዲጠብቅ፥ በዚህም መጽሐፍ የተጻፈውን የቃል ኪዳን ቃል እንዲያደርግ በጌታ ፊት ቃል ኪዳን አደረገ።

Ver Capítulo Copiar

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

31 ንጉሡ በዐምዱ አጠገብ ቆሞ በሙሉ ልቡና ሐሳቡ እግዚአብሔርን ለመከተልና ትእዛዞቹን፥ ደንቦቹንና ድንጋጌዎቹን ለመጠበቅ በእርሱ ፊት ቃል ኪዳኑን አደሰ፤ ስለዚህም በዚህ መጽሐፍ የተጻፈውን ቃል ኪዳን አረጋገጠ።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

31 ንጉሡም በስፍራው ቆሞ እግዚአብሔርን ተከትሎ እንዲሄድ፥ ትእዛዙንና ምስክሩን፥ ሥርዓቱንም በፍጹም ልቡና በፍጹም ነፍሱ እንዲጠብቅ፥ በዚህም መጽሐፍ የተጻፈውን የቃል ኪዳን ቃል እንዲያደርግ በእግዚአብሔር ፊት ቃል ኪዳን አደረገ።

Ver Capítulo Copiar




2 ዜና መዋዕል 34:31
30 Referencias Cruzadas  

እነ​ሆም፥ ንጉ​ሡን እንደ ተለ​መ​ደው በዓ​ምዱ አጠ​ገብ ቆሞ፥ ከን​ጉ​ሡም ጋር መዘ​ም​ራ​ንና መለ​ከ​ተ​ኞች ቆመው አየች፤ የሀ​ገ​ሩም ሕዝብ ሁሉ ደስ ብሎ​አ​ቸው መለ​ከት ይነፉ ነበር። ጎቶ​ል​ያም ልብ​ስ​ዋን ቀድዳ፥ “ዐመፅ ነው፥ ዐመፅ ነው፥” ብላ ጮኸች።


ዮዳ​ሄም የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሕዝብ ይሆኑ ዘንድ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርና በን​ጉሡ፥ በሕ​ዝ​ቡም መካ​ከል ቃል ኪዳን አደ​ረገ፤ ደግ​ሞም በን​ጉ​ሡና በሕ​ዝቡ መካ​ከል ቃል ኪዳን አደ​ረገ።


በሰ​ባ​ተ​ኛ​ውም ዓመት ዮዳሄ ልኮ፥ በኮ​ራ​ው​ያ​ንና በዘ​በ​ኞች ላይ ያሉ​ትን የመቶ አለ​ቆች ወሰደ፤ ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ቤት አገ​ባ​ቸው፤ ከእ​ነ​ር​ሱም ጋር የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቃል ኪዳን አደ​ረገ፤ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ቤት አማ​ላ​ቸው፤ የን​ጉ​ሡ​ንም ልጅ አሳ​ያ​ቸው።


ንጉ​ሡም በዓ​ምደ ወርቁ አጠ​ገብ ቆሞ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ይከ​ተሉ ዘንድ፥ ትእ​ዛ​ዙ​ንና ምስ​ክ​ሩ​ንም ሥር​ዐ​ቱ​ንም በፍ​ጹም ልባ​ቸ​ውና በፍ​ጹም ነፍ​ሳ​ቸው ይጠ​ብቁ ዘንድ፥ በዚ​ህም መጽ​ሐፍ የተ​ጻ​ፈ​ውን የቃል ኪዳን ቃል ያጸኑ ዘንድ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ቃል ኪዳን አደ​ረገ፤ ሕዝ​ቡም ሁሉ በቃል ኪዳን ጸኑ።


በፍ​ጹም ልባ​ቸ​ውና በፍ​ጹም ነፍ​ሳ​ቸው የአ​ባ​ቶ​ቻ​ቸ​ውን አም​ላክ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ይሹ ዘንድ ቃል ኪዳን አደ​ረገ፤


በፍ​ጹ​ምም ልባ​ቸው ምለ​ዋ​ልና፥ በፍ​ጹ​ምም ሕሊ​ና​ቸው ፈል​ገ​ው​ታ​ልና፥ እር​ሱም ተገ​ኝ​ቶ​ላ​ቸ​ዋ​ልና ይሁዳ ሁሉ በመ​ሐ​ላው ደስ አላ​ቸው፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በዙ​ሪ​ያ​ቸው ዕረ​ፍ​ትን ሰጣ​ቸው።


ካህኑ ኢዮ​አ​ዳም በእ​ር​ሱና በሕ​ዝቡ ሁሉ፥ በን​ጉ​ሡም መካ​ከል የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሕዝብ ይሆኑ ዘንድ ቃል ኪዳን አደ​ረገ።


አሁ​ንም የቍ​ጣ​ውን መቅ​ሠ​ፍት ከእኛ እን​ዲ​መ​ልስ ከእ​ስ​ራ​ኤል አም​ላክ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጋር ቃል ኪዳን አደ​ርግ ዘንድ በልቤ አስ​ቤ​አ​ለሁ።


እንደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ሰው እንደ ሙሴ ሕግ በቦ​ታ​ቸ​ውና በሥ​ር​ዐ​ታ​ቸው ቆሙ፤ ካህ​ና​ቱም ከሌ​ዋ​ው​ያን እጅ የተ​ቀ​በ​ሉ​ትን ደም ይረጩ ነበር።


ስለ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ቤት አገ​ል​ግ​ሎት በጀ​መ​ረው ሥራ ሁሉ፥ በሕ​ጉና በት​እ​ዛ​ዙም አም​ላ​ኩን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን በፍ​ጹም ልቡ ፈለ​ገው፤ ሥራ​ውም ሁሉ ተከ​ና​ወ​ነ​ለት።


በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምና በብ​ን​ያ​ምም ሀገር የተ​ገ​ኙ​ትን ሁሉ በዚህ ነገር አማለ። በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም የሚ​ኖሩ እንደ አባ​ቶ​ቻ​ቸው አም​ላክ እንደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት ቃል ኪዳን አደ​ረጉ።


ሰሎ​ሞ​ንም ርዝ​መቱ አም​ስት ክንድ፥ ወር​ዱም አም​ስት ክንድ፥ ቁመ​ቱም ሦስት ክንድ የሆነ የናስ መድ​ረክ ሠርቶ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት አደ​ባ​ባይ መካ​ከል ተክ​ሎት ነበር፤ በላ​ዩም ቆመ፤ በእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ጉባኤ ሁሉ ፊት በጕ​ል​በቱ ተን​በ​ር​ክኮ እጁን ወደ ሰማይ ዘረጋ፤


አሁ​ንም እንደ ጌታ​ዬና የአ​ም​ላ​ካ​ች​ንን ትእ​ዛዝ እን​ደ​ሚ​ፈ​ሩት ምክር፥ ሴቶ​ችን ሁሉ፥ ከእ​ነ​ር​ሱም የተ​ወ​ለ​ዱ​ትን እን​ሰ​ድድ ዘንድ ከአ​ም​ላ​ካ​ችን ጋር ቃል ኪዳን እና​ድ​ርግ። ተነሥ እንደ አም​ላ​ካ​ች​ንም ትእ​ዛዝ ገሥ​ፃ​ቸው፤ እንደ ሕጉም ያድ​ርጉ፤


በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ባሪያ በሙሴ እጅ በተ​ሰ​ጠው በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሕግ ይሄዱ ዘንድ፥ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ትእ​ዛዝ ሁሉ፥ ፍር​ዱ​ንም፥ ሥር​ዐ​ቱ​ንም ይጠ​ብ​ቁና ያደ​ርጉ ዘንድ ርግ​ማ​ን​ንና መሐ​ላን አደ​ረጉ።


ሴቶች ልጆ​ቻ​ች​ን​ንም ለም​ድር አሕ​ዛብ አን​ሰ​ጥም፤ ሴቶች ልጆ​ቻ​ቸ​ው​ንም ለል​ጆ​ቻ​ችን አን​ወ​ስ​ድም፤


ስለ​ዚ​ህም ሁሉ የታ​መ​ነ​ውን ቃል ኪዳን አድ​ር​ገን እን​ጽ​ፋ​ለን፤ አለ​ቆ​ቻ​ች​ንም፥ ሌዋ​ው​ያ​ኖ​ቻ​ች​ንም፥ ካህ​ና​ቶ​ቻ​ች​ንም ያት​ሙ​በ​ታል።”


ወደ ጽዮን የሚ​ሄ​ዱ​በ​ትን ጎዳና ይመ​ረ​ም​ራሉ፤ ፊታ​ቸ​ው​ንም ወደ ሀገ​ራ​ቸው ይመ​ል​ሳሉ፤ የዘ​ለ​ዓ​ለም ቃል​ኪ​ዳን አይ​ረ​ሳ​ምና መጥ​ተው ወደ ፈጣ​ሪ​ያ​ቸው ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይማ​ጠ​ናሉ።


አለ​ቃው በስተ ውጭ ባለው በር በደጀ ሰላሙ መን​ገድ ገብቶ በበሩ መቃን አጠ​ገብ ይቁም፤ ካህ​ና​ቱም የእ​ር​ሱን የሚ​ቃ​ጠ​ለ​ውን መሥ​ዋ​ዕ​ትና የደ​ኅ​ን​ነ​ቱን መሥ​ዋ​ዕት ያቅ​ርቡ፥ እር​ሱም በበሩ መድ​ረክ ላይ ይስ​ገድ፤ ከዚ​ያም በኋላ ይውጣ፤ በሩ ግን እስከ ማታ ድረስ አይ​ዘጋ።


አም​ላ​ካ​ች​ሁን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ተከ​ተሉ፤ እር​ሱ​ንም ፍሩ፤ ትእ​ዛ​ዙ​ንም ጠብቁ፤ ቃሉ​ንም ስሙ፥ እር​ሱ​ንም ተማ​ጠ​ኑት።


ከግ​ብፅ ምድር ካወ​ጣ​ችሁ፥ ከባ​ር​ነ​ትም ቤት ካዳ​ና​ችሁ ከአ​ም​ላ​ካ​ችሁ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሊያ​ስ​ታ​ችሁ፥ አም​ላ​ክህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ትሄ​ድ​ባት ዘንድ ካዘ​ዘህ መን​ገድ ሊያ​ወ​ጣህ ተና​ግ​ሮ​አ​ልና ያ ነቢይ ወይም ሕልም አላሚ ይገ​ደል፤ እን​ዲ​ሁም ክፉ​ውን ነገር ከአ​ንተ አርቅ።


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በኮ​ሬብ ካደ​ረ​ገው ቃል ኪዳን ሌላ በሞ​ዓብ ምድር ከእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ጋር ያደ​ር​ገው ዘንድ ሙሴን ያዘ​ዘው የቃል ኪዳኑ ቃሎች እነ​ዚህ ናቸው።


አም​ላ​ክ​ህ​ንም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን በፍ​ጹም ልብህ፥ በፍ​ጹ​ምም ነፍ​ስህ፥ በፍ​ጹ​ምም ኀይ​ልህ ውደድ።


በዚ​ያም ቀን ኢያሱ ከሕ​ዝቡ ጋር ቃል ኪዳን አደ​ረገ፤ በሴ​ሎም በእ​ስ​ራ​ኤል አም​ላክ ድን​ኳን ፊት ሕግ​ንና ፍር​ድን ሰጣ​ቸው።


Síguenos en:

Anuncios


Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos