Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -




1 ሳሙኤል 20:21 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

21 እነ​ሆም፦ ሂድ ፍላ​ጻ​ዎ​ቹን ፈልግ ብዬ ብላ​ቴ​ና​ውን እል​ካ​ለሁ፤ ብላ​ቴ​ና​ው​ንም፦ እነሆ፥ ፍላ​ጻው ከአ​ንተ ወደ​ዚህ ነው፤ ይዘ​ኸው ወደ እኔ ና ያል​ሁት እንደ ሆነ፥ ሕያው እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን! ለአ​ንተ ሰላም ነውና ምንም ክፉ ነገር የለ​ብ​ህም።

Ver Capítulo Copiar

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

21 ከዚያም፣ ‘ሂድና ፍላጾቹን አምጣቸው’ ብዬ አንድ ልጅ እልካለሁ፤ ልጁንም፣ ‘እነሆ፤ ፍላጾቹ ያሉት፣ ከአንተ ወደዚህ ነው፤ ሄደህ አምጣቸው’ ያልሁት እንደ ሆነ፣ ሕያው እግዚአብሔርን! ክፉ ነገር አያገኝህም፤ አደጋም የለም፤ ውጣና ና።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

21 ከዚያም፥ ‘ሂድና ፍላጾቹን አምጣቸው’ ብዬ አንድ ልጅ እልካለሁ፤ ልጁንም፥ ‘እነሆ፤ ፍላጾቹ ያሉት፥ ከአንተ ወደዚህ ነው፤ ሄደህ አምጣቸው’ ያልሁት እንደሆነ፥ በሕያው ጌታ ስም! ክፉ ነገር አያገኝህም፤ ውጣና ና፤ አደጋ እንደማይኖርም እምልልሃለሁ።

Ver Capítulo Copiar

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

21 ከዚያም በኋላ ፍላጻዎቹን እንዲያመጣ ልጁን እልካለሁ፤ ‘ፍላጻዎቹ ከአንተ ወደዚህ ናቸውና አምጣቸው!’ ካልሁት አንተ ከተደበቅኽበት ቦታ ልትወጣ ትችላለህ፤ ስለዚህ ምንም ችግር እንደማይደርስብህና ምንም አደጋ እንደሌለ በእግዚአብሔር ስም እምልልሃለሁ።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

21 እነሆም፦ ሂድ ፍላጻዎችን ፈልግ ብዬ ብላቴናውን እልከዋለሁ፥ ብላቴናውንም፦ እነሆ፥ ፍላጻው ከአንተ ወደዚህ ነው፥ ይዘኸው ወደ እኔ ና ያልሁት እንደ ሆነ፥ ሕያው እግዚአብሔርን! ለአንተ ደኅንነት ነውና ምንም የለብህም።

Ver Capítulo Copiar




1 ሳሙኤል 20:21
7 Referencias Cruzadas  

በበ​ዓል ይምሉ ዘንድ ሕዝ​ቤን እን​ዳ​ስ​ተ​ማሩ በስሜ፦ ሕያው እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን! ብለው ይምሉ ዘንድ የሕ​ዝ​ቤን መን​ገድ ፈጽ​መው ቢማሩ፥ በዚያ ጊዜ በሕ​ዝቤ መካ​ከል ይመ​ሠ​ረ​ታሉ።


ሕያው እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን! ብሎ በእ​ው​ነ​ትና በቅ​ን​ነት፤ በጽ​ድ​ቅም ቢምል፥ አሕ​ዛብ በእ​ርሱ ይባ​ረ​ካሉ፤ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ያመ​ሰ​ግ​ናሉ።


እነ​ር​ሱም፦ ሕያው እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን! ቢሉ የሚ​ም​ሉት በሐ​ሰት ነው።”


ዳን ሆይ፥ ሕያው አም​ላ​ክ​ህን! ደግ​ሞም፦ ሕያው የቤ​ር​ሳ​ቤ​ህን አም​ላክ ብለው በሰ​ማ​ርያ መማ​ፀኛ የሚ​ምሉ፥ እነ​ርሱ ይወ​ድ​ቃሉ፥ ደግ​ሞም አይ​ነ​ሡም።”


እኔም በዓ​ላማ ላይ እወ​ረ​ው​ራ​ለሁ ብዬ ሦስት ፍላ​ጻ​ዎ​ችን ወደ ዓላ​ማው እወ​ረ​ው​ራ​ለሁ።


ብላ​ቴ​ና​ውን ግን፦ እነሆ፥ ፍላ​ጻው ከአ​ንተ ወዲያ ነው ያል​ሁት እንደ ሆነ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አሰ​ና​ብ​ቶ​ሃ​ልና መን​ገ​ድ​ህን ሂድ።


ብላ​ቴ​ና​ው​ንም፥ “ሮጠህ የም​ወ​ረ​ው​ራ​ቸ​ውን ፍላ​ጻ​ዎች ፈል​ግ​ልኝ” አለው። ብላ​ቴ​ና​ውም በሮጠ ጊዜ ዮና​ታን ፍላ​ጻ​ውን ወደ ማዶ አሳ​ልፎ ወረ​ወ​ረው።


Síguenos en:

Anuncios


Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos