Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -




1 ነገሥት 17:19 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

19 ኤል​ያ​ስም፥ “ልጅ​ሽን ስጪኝ” አላት፥ ከብ​ብ​ቷም ወስዶ ተቀ​ም​ጦ​በት ወደ ነበ​ረው ሰገ​ነት አወ​ጣው፤ በአ​ል​ጋ​ውም ላይ አስ​ተ​ኛው።

Ver Capítulo Copiar

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

19 ኤልያስም መልሶ፣ “ልጅሽን ስጪኝ” አላት፤ ልጁንም ከዕቅፏ ወስዶ እርሱ ወደሚኖርበት ሰገነት በማውጣት በዐልጋው ላይ አስተኛው።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

19 ኤልያስም “ልጅሽን ወደ እኔ አምጪው” አላት። ልጁንም ከዕቅፍዋ ወስዶ እርሱ ወደሚኖርበት ሰገነት አውጥቶ በአልጋው ላይ አጋደመው።

Ver Capítulo Copiar

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

19 ኤልያስም “ልጅሽን ወደ እኔ አምጪው” አላት። ልጁንም ከዕቅፍዋ ወስዶ እርሱ ወደሚኖርበት ሰገነት አውጥቶ በአልጋው ላይ አጋደመው፤

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

19 ኤልያስም “ልጅሽን ስጪኝ፤” አላት። ከብብትዋም ወስዶ ተቀምጦበት ወደ ነበረው ሰገነት አወጣው፤ በአልጋውም ላይ አጋደመው።

Ver Capítulo Copiar




1 ነገሥት 17:19
6 Referencias Cruzadas  

እር​ስ​ዋም ኤል​ያ​ስን፥ “የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሰው ሆይ፥ እኔ ከአ​ንተ ጋር ምን አለኝ? አን​ተስ ከእኔ ጋር ምን አለህ? ኀጢ​አ​ቴ​ንስ ታሳ​ስብ ዘንድ፥ ልጄ​ንስ ትገ​ድል ዘንድ ወደ እኔ መጥ​ተ​ሃ​ልን?” አለ​ችው።


ኤል​ያ​ስም፥ “እኔ በቤቷ ያደ​ርሁ የዚች መበ​ለት ምስ​ክ​ርዋ ጌታዬ ሆይ፥ ልጅ​ዋን በመ​ግ​ደ​ልህ ክፉ አድ​ር​ገ​ህ​ባ​ታ​ልና ወዮ​ልኝ!” ብሎ ጮኸ።


ትንሽ ቤት በሰ​ገ​ነቱ ላይ እን​ሥራ፤ በዚ​ያም አል​ጋና ጠረ​ጴዛ፥ ወን​በ​ርና መቅ​ረዝ እና​ኑ​ር​ለት፤ ወደ እኛም ሲመጣ ወደ​ዚያ ይግባ” አለ​ችው።


አው​ጥ​ታም በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሰው አልጋ ላይ አጋ​ደ​መ​ችው፤ በሩ​ንም ዘግ​ታ​በት ወጣች።


ኤል​ሳ​ዕም ወደ ቤት በገባ ጊዜ እነሆ፥ ሕፃኑ ሞቶ በአ​ል​ጋው ላይ ተጋ​ድሞ ነበር።


ያን​ጊ​ዜም ታማ ሞተ​ችና በድ​ን​ዋን አጥ​በው በሰ​ገ​ነት አስ​ተ​ኙ​አት።


Síguenos en:

Anuncios


Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos