Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -




1 ዜና መዋዕል 5:1 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም በኵር የሮ​ቤል ልጆች እነ​ዚህ ናቸው። እርሱ የበ​ኵር ልጅ ነበረ፤ ነገር ግን ወደ አባቱ ምን​ጣፍ ስለ ወጣ አባቱ እስ​ራ​ኤል በረ​ከ​ቱን ለልጁ ለዮ​ሴፍ ሰጠ፤ ብኵ​ር​ናም አል​ተ​ቈ​ጠ​ረ​ለ​ትም።

Ver Capítulo Copiar

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

1 የእስራኤል የበኵር ልጅ የሮቤል ልጆች፤ ሮቤል የበኵር ልጅ ቢሆንም፣ የአባቱን መኝታ ስላረከሰ፣ የብኵርና መብቱ ለእስራኤል ልጅ ለዮሴፍ ልጆች ተሰጥቷል። ከዚህም የተነሣ ትውልዱ የበኵርነቱን ተራ ይዞ ሊቈጠር አልቻለም።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

1 የእስራኤልም በኩር የሮቤል ልጆች እነዚህ ናቸው። እርሱ የበኩር ልጅ ነበረ፤ ነገር ግን የአባቱን ምንጣፍ ስላረከሰ ብኩርናው ለእስራኤል ልጅ ለዮሴፍ ልጆች ተሰጠ፤ ትውልዱ ግን ከብኩርናው ጋር አልተቈጠረም።

Ver Capítulo Copiar

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

1 የያዕቆብ የበኲር ልጅ የሆነው የሮቤል ዘሮች ቀጥሎ የተመለከቱት ናቸው፤ (ሮቤል የአባቱን አልጋ ደፍሮ በማርከሱ የብኲርናውን መብት ስላጣ፥ ያ መብት ለዮሴፍ ተሰጥቶ ነበር፤

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

1 የእስራኤልም በኵር የሮቤል ልጆች እነዚህ ናቸው። እርሱ የበኵር ልጅ ነበረ፤ ነገር ግን የአባቱን ምንጣፍ ስላረከሰ ብኵርናው ለእስራኤል ልጅ ለዮሴፍ ልጆች ተሰጠ፤ ትውልዱ ግን ከብኵርና ጋር አልተቈጠረም።

Ver Capítulo Copiar




1 ዜና መዋዕል 5:1
23 Referencias Cruzadas  

እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም አላት፥ “ሁለት ሕዝ​ቦች በማ​ኅ​ፀ​ንሽ አሉ፤ ሁለ​ቱም ሕዝብ ከሆ​ድሽ ይወ​ለ​ዳሉ፤ ሕዝ​ብም ከሕ​ዝብ ይበ​ረ​ታል፤ ታላ​ቁም ለታ​ናሹ ይገ​ዛል።”


ያዕ​ቆ​ብም ዔሳ​ውን፥ “ዛሬ ብኵ​ር​ና​ህን ስጠኝ” አለው።


ልያም ፀነ​ሰች፤ ወንድ ልጅ​ንም ወለ​ደች፥ ስሙ​ንም ሮቤል ብላ ጠራ​ችው፥ “እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መዋ​ረ​ዴን አይ​ቶ​አ​ልና፥ እን​ግ​ዲ​ህስ ወዲህ ባሌ ይወ​ድ​ደ​ኛል” ስትል።


የያ​ዕ​ቆ​ብም ልጆች ዐሥራ ሁለት ናቸው፤


ከአ​ባ​ታ​ቸው ከያ​ዕ​ቆብ ጋር ወደ ግብፅ የገ​ቡት የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ስም ይህ ነው፤ ያዕ​ቆ​ብና ልጆቹ፤ የያ​ዕ​ቆብ በኵር ሮቤል።


አሁ​ንም እኔ ወደ አንተ ከመ​ም​ጣቴ በፊት በግ​ብፅ ምድር የተ​ወ​ለ​ዱ​ልህ ሁለቱ ልጆ​ችህ ለእኔ ይሁኑ፤ ኤፍ​ሬ​ምና ምናሴ ለእኔ እንደ ሮቤ​ልና እንደ ስም​ዖን ናቸው።


የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ልጆች ስሞች እነ​ዚህ ናቸው፤ ሮቤል፥ ስም​ዖን፥ ሌዊ፥ ይሁዳ፥ ይሳ​ኮር፥ ዛብ​ሎን፤


ከሜ​ራ​ሪም ልጆች ለነ​በ​ረው ለሖሳ ፊተ​ኛ​ውን በር የሚ​ጠ​ብቁ ልጆች ነበ​ሩት፤ አለ​ቃ​ውም ሰምሪ ነበረ፤ በኵር አል​ነ​በ​ረም፤ አባቱ ግን አለቃ አደ​ረ​ገው፤


የአ​ባ​ቶ​ቻ​ቸ​ውም ቤት አለ​ቆች እነ​ዚህ ናቸው። የእ​ስ​ራ​ኤል የበ​ኵር ልጅ የሮ​ቤል ልጆች ሄኖኅ፥ ፍሉስ፥ አስ​ሮን፥ ከርሚ፤ እነ​ዚህ የሮ​ቤል ትው​ልድ ናቸው።


የአ​ባ​ት​ህን ሚስት ኀፍ​ረተ ሥጋ አት​ግ​ለጥ፤ የአ​ባ​ትህ ኀፍ​ረተ ሥጋ ነው።


ማና​ቸ​ውም ሰው ከአ​ባቱ ሚስት ጋር ቢተኛ የአ​ባ​ቱን ኀፍ​ረተ ሥጋ ገል​ጦ​አል፤ ሁለ​ቱም ፈጽ​መው ይገ​ደሉ፤ በደ​ለ​ኞች ናቸው።


ከእ​ና​ን​ተም ጋር የሚ​ቆ​ሙት ሰዎች ስሞ​ቻ​ቸው እነ​ዚህ ናቸው፤ ከሮ​ቤል የሰ​ዲ​ዮር ልጅ ኤሊ​ሱር፥


የሌ​ዊም ልጅ የቀ​ዓት ልጅ የይ​ስ​ዓር ልጅ ቆሬ ከኤ​ል​ያብ ልጆች ከዳ​ታ​ንና ከአ​ቤ​ሮን፥ ከሮ​ቤ​ልም ልጅ ከፋ​ሌት ልጅ ከአ​ው​ናን ጋር ተና​ገረ።


የእ​ስ​ራ​ኤል በኵር ሮቤል፤ የሮ​ቤል ልጆች፤ ከሄ​ኖኅ የሄ​ኖ​ኃ​ው​ያን ወገን፤ ከፈ​ሉስ የፈ​ሉ​ሳ​ው​ያን ወገን።


በእ​ና​ንተ ላይ ዝሙት ይሰ​ማል፤ እን​ደ​ዚህ ያለው ዝሙ​ትም አረ​ማ​ው​ያን እንኳ የማ​ያ​ደ​ር​ጉት ነው፤ ያባ​ቱን ሚስት ያገባ አለና።


ነገር ግን ከከ​ብቱ ሁለት እጥፍ ለእ​ርሱ በመ​ስ​ጠት ከተ​ጠ​ላ​ችው ሚስት የተ​ወ​ለ​ደው ልጅ በኵር እንደ ሆነ ያስ​ታ​ውቅ። የኀ​ይሉ መጀ​መ​ሪያ ነውና በኵ​ር​ነቱ የእ​ርሱ ነው።


“ከእ​ን​ጀራ እናቱ ጋር የሚ​ተኛ የአ​ባ​ቱን ኀፍ​ረት ገል​ጦ​አ​ልና ርጉም ይሁን፤ ሕዝ​ቡም ሁሉ አሜን ይላሉ።


ውበቱ እንደ ላም በኵር ነው፤ ቀን​ዶቹ አንድ ቀንድ እን​ዳ​ለው ናቸው፤ በእ​ነ​ርሱ እስከ ምድር ዳርቻ ያሉ​ትን አሕ​ዛብ ሁሉ ይወ​ጋል፤ የኤ​ፍ​ሬም እልፍ አእ​ላ​ፋት፥ የም​ና​ሴም አእ​ላ​ፋት እነ​ርሱ ናቸው።


ይኸ​ውም የማ​ይ​ታይ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የሚ​መ​ስ​ለው፥ ከፍ​ጥ​ረቱ ሁሉ በላይ የሆነ በኵር ነው።


የይ​ሁ​ዳም ልጆች በጌ​ል​ገላ ወደ ኢያሱ ቀረቡ፤ ቄኔ​ዛ​ዊ​ውም የዮ​ፎኒ ልጅ ካሌብ አለው፥ “ለአ​ም​ላክ ሰው ለሙሴ ስለ እኔና ስለ አንተ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በቃ​ዴስ በርኔ የተ​ና​ገ​ረ​ውን ቃል ታው​ቃ​ለህ።


Síguenos en:

Anuncios


Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos