Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -




ኢያሱ 19:47 - አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

47 የዳንም ሕዝብ ይህን ምድር ለመውረስ የማይቻል ሆኖ ባገኙት ጊዜ ወደ ላዪሽ ሄደው አደጋ በመጣል ከተማይቱን ያዙ፤ ሕዝብዋንም ፈጅተው የራሳቸው ይዞታ አደረጉአት፤ በዚያም ሰፈሩ፤ ላዪሽ ትባል የነበረችውን ከተማ ስሟን ለውጠው በቀድሞ አባታቸው ስም ዳን ብለው ጠሩአት፤

Ver Capítulo Copiar

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

47 ነገር ግን የዳን ዘሮች ርስታቸው አልበቃቸውም፣ ወደ ሌሼም ወጥተው አደጋ በመጣል ያዟት፤ ሰዎቹንም በሰይፍ ስለት ፈጅተው ይዞታቸው አደረጓት፤ በዚያው ሰፈሩ፤ ስሟንም ለውጠው በአባታቸው ስም ዳን አሏት።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

47 የዳንም ልጆች ግዛታቸውን መቆጣጠር ባለልቻሉ ጊዜ ከሌሼም ጋር ሊዋጉ ወጡ፥ ያዙአትም፥ በሰይፍም ስለት መቱአት፥ ወረሱአትም፥ ተቀመጡባትም፤ ሌሼም የነበረውን ስምዋንም በአባታቸው በዳን ስም ዳን ብለው ጠሩአት።

Ver Capítulo Copiar

የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

47 የዳን ልጆች ነገድ ርስት በየ​ወ​ገ​ኖ​ቻ​ቸው እነ​ዚህ ከተ​ሞ​ችና መን​ደ​ሮ​ቻ​ቸው ናቸው። የዳን ልጆ​ችም በተ​ራ​ራው ላይ የሚ​ያ​ስ​ጨ​ን​ቋ​ቸው አሞ​ሬ​ዎ​ና​ው​ያ​ንን አላ​ስ​ጨ​ነ​ቁ​አ​ቸ​ውም። አሞ​ሬ​ዎ​ና​ው​ያ​ንም ወደ ሸለ​ቆ​ዎች ይወ​ርዱ ዘንድ አል​ፈ​ቀ​ዱ​ላ​ቸ​ውም። ከእ​ነ​ር​ሱም ከር​ስ​ታ​ቸው ዳርቻ አንድ ክፍ​ልን ወሰዱ።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

47 የዳንም ልጆች ዳርቻ አልበቃቸውም፥ የዳንም ልጆች ከሌሼም ጋር ሊዋጉ ወጡ፥ ያዙአትም፥ በሰይፍም ስለት መቱአት፥ ወረሱአትም፥ ተቀመጡባትም፥ ስምዋንም በአባታቸው በዳን ስም ዳን ብለው ጠሩአት።

Ver Capítulo Copiar




ኢያሱ 19:47
6 Referencias Cruzadas  

ቀጥለውም ወደ ገለዓድና በሒታውያን ግዛት ውስጥ ወዳለው ወደ ቃዴስ ዘለቁ፤ ከዚያም በኋላ ወደ ዳን፥ ከዳንም ወደ ምዕራብ ታጥፈው ወደ ሲዶና ሄዱ፤


ስለ ዳንም ነገድ እንዲህ አለ፦ “ዳን እንደ አንበሳ ደቦል ነው፤ እርሱ ከባሳን ይዘላል።”


ሜያርቆን፥ ራቆንና እንዲሁም በኢዮጴ ዙሪያ ያለውን ግዛት ጭምር ያጠቃልላል።


ስለዚህ እነዚህ ትላልቅና ትናንሽ ከተሞች የዳን ልጆች በየወገናቸው ርስት ናቸው።


Síguenos en:

Anuncios


Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos