Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -




ዕዝራ 2:3 - አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

3-20 ከፓርዖሽ ወገን 2172 ከሸፋጥያ ወገን 372 ከአራሕ ወገን 775 ከፓሐትሞአብ ወገን የኢያሱና የኢዮአብ ዘሮች 2812 ከዔላም ወገን 1254 ከዛቱ ወገን 945 ከዛካይ ወገን 760 ከባኒ ወገን 642 ከቤባይ ወገን 623 ከዓዝጋድ ወገን 1222 ከአዶኒቃም ወገን 666 ከቢግዋይ ወገን 2056 ከዓዲን ወገን 454 በሕዝቅያስ በኩል ከአጤር ወገን 98 ከቤጻይ ወገን 323 ከዮራ ወገን 112 ከሐሹም ወገን 223 ከጊባር ወገን 95

Ver Capítulo Copiar

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

3 የፋሮስ ዘሮች 2,172

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

3 የፓርዖሽ ልጆች፥ ሁለት ሺህ አንድ መቶ ሰባ ሁለት።

Ver Capítulo Copiar

የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

3 የፋ​ሮስ ልጆች ሁለት ሺህ መቶ ሰባ ሁለት።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

3 የፋሮስ ልጆች፥ ሁለት ሺህ መቶ ሰባ ሁለት።

Ver Capítulo Copiar




ዕዝራ 2:3
8 Referencias Cruzadas  

ከሌሎች እስራኤላውያን፦ ከፓርዖሽ ጐሣ፦ ራምያ፥ ይዚያ፥ ማልኪያ፥ ሚያሚን፥ አልዓዛር ማልኪያና በናያ፤


ለተመለሱትም ስደተኞች መሪዎች ሆነው የመጡት ዘሩባቤል፥ ኢያሱ፥ ነህምያ፥ ሠራያ፥ ረዔላያ፥ መርዶክዮስ፥ ቢልሻን፥ ሚስፓር፥ ቢግዋይ፥ ሬሁምና በዓና ተብለው የሚጠሩት ነበሩ። ከእያንዳንዱ እስራኤላዊ ጐሣ በመሰባሰብ ወደ ሀገር የተመለሱትም ስደተኞች ዝርዝር ከዚህ የሚከተለው ነው፦


በንጉሡ በአርጤክስስ ዘመነ መንግሥት ከእኔ ጋር ከባቢሎን የተመለሱት የቤተሰብ አለቆች በየትውልዳቸው እንደሚከተለው ነው፦


የዑዛይ ልጅ ፓላል ከቅጽሩ ማእዘንና በዘብ መጠበቂያው አደባባይ አጠገብ ከሚገኘው ከላይኛው ቤተ መንግሥት መጠበቂያ ግንብ ጀምሮ ያለውን ክፍል ሁሉ ሠራ። የፓርዖሽ ልጅ ፐዳያ ደግሞ በውሃው ቅጽር በር አጠገብ ወደምሥራቅ የሚያመለክተውን ስፍራና የቤተ መቅደሱን መጠበቂያ ግንብ ይኸውም የቤተ መቅደሱ ሠራተኞች በሚኖሩበት የከተማይቱ አንድ ክፍል በሆነው “ዖፌል” ተብሎ በሚጠራው ስፍራ አጠገብ ያለውን ክፍል ሠራ።


ከምርኮ ከተመለሱት ከእያንዳንዱ ጐሣ ተወጣጥተው የተመዘገቡት የእስራኤል ጐሣዎችና የትውልዳቸው ብዛት ይህ ነው፦ ከፓርዖሽ ወገን የተመዘገቡ 2172 ከሸፋጥያ ወገን የተመዘገቡ 372 ከአራሕ ወገን የተመዘገቡ 652 የኢያሱና የኢዮአብ ትውልድ ጐሣ ከሆነው ከፓሐትሞአብ ወገን የተመዘገቡ 2818 ከዔላም ወገን የተመዘገቡ 1254 ከዛቱ ወገን የተመዘገቡ 845 ከዛካይ ወገን የተመዘገቡ 760 ከቢኑይ ወገን የተመዘገቡ 648 ከቤባይ ወገን የተመዘገቡ 628 ከዓዝጋድ ወገን የተመዘገቡ 2322 ከአዶኒቃም ወገን የተመዘገቡ 667 ከቢግዋይ ወገን የተመዘገቡ 2067 ከዓዲን ወገን የተመዘገቡ 655 ሕዝቅያስ ተብሎ ከሚጠራው ከአጤር ወገን የተመዘገቡ 98 ከሐሹም ወገን የተመዘገቡ 328 ከቤጻይ ወገን የተመዘገቡ 324 ከሐሪፍ ወገን የተመዘገቡ 112 ከገባዖን ወገን የተመዘገቡ 95


Síguenos en:

Anuncios


Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos