Biblia Todo Logo
La Biblia Online

- Anuncios -




ምሳሌ 23:31 - መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

31 ወደ ወይን ጠጅ አትመልከት ሲቀላ፥ መልኩም በብርጭቆ ሲያንጸባርቅ፥ እየጣፈጠም ሲገባ።

Ver Capítulo Copiar

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

31 መልኩ ቀይ ሆኖ፣ በብርጭቆ ውስጥ ሲያንጸባርቅ፣ ሰተት ብሎ በሚወርድበትም ጊዜ፣ ወደ ወይን ጠጅ ትክ ብለህ አትመልከት።

Ver Capítulo Copiar

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

31 ስለዚህ ምንም እንኳ መልኩ በጣም ቀይ ሆኖ በብርጭቆ ውስጥ ቢያንጸባርቅ ሲጠጡትም ሰተት ብሎ ቢገባ የወይን ጠጅ አያስጐምጅህ።

Ver Capítulo Copiar

የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

31 ወደ ጽዋዎችና ወደ ብርሌ ዐይንህን ብትሰጥ፥ በኋላ እንደ ግንብ ዕራቁትህን ትሄዳለህ፤

Ver Capítulo Copiar




ምሳሌ 23:31
9 Referencias Cruzadas  

ምክንያቱም በዓለም ያለው ሁሉ፥ የሥጋ ምኞት፥ የዐይን ምኞት፥ በኑሮ ደረጃ መመካት፥ ከዓለም ነው እንጂ ከአብ አይደለም።


ከንቱ ነገርን እንዳያዩ ዐይኖቼን መልስ፥ በመንገድህ ሕያው አድርገኝ።


አንድ ቀን ማታ፥ ዳዊት ከአልጋው ተነሥቶ በቤተ መንግሥቱ ሰገነት ወዲያና ወዲህ ይመላለስ ነበር፤ ከሰገነቱ ላይ እንዳለም፥ አንዲት ሴት ገላዋን ስትታጠብ አየ፤ ሴቲቱም እጅግ ውብ ነበረች።


ዐይንህ ብታሰናክልህ ጐልጉለህ አውጣት፤ ሁለት ዐይን ኖሮህ ወደ ገሃነም ከመጣል፥ አንድ ዐይን ኖሮህ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት መግባት ይሻልሃል፤


ውበትዋን በልብህ አትመኘው፥ በዐይኖችዋም አትማረክ።


“እንግዲህ፥ ኢዮብ ሆይ፥ ንግግሬን እንድትሰማ፥ ቃሌንም ሁሉ እንድታደምጥ እለምንሃለሁ።


መንፈስ ይሙላባችሁ እንጂ ብክነት እንደ ሆነው በወይን ጠጅ አትስከሩ፤


አፍሽ ለወዳጄ እየጣፈጠ እንደሚገባ፥ የተኙትን ከንፈሮች ይናገሩ ዘንድ እንደሚያደርግ፥ እንደ ማለፊያ የወይን ጠጅ ነው።


Síguenos en:

Anuncios


Anuncios