ሕዝቅኤል 45:14 - መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)14 የዘይቱም ደንብ፥ ከእያንዳንዱ የቆሮስ መስፈሪያ የባዶስን አንድ አሥረኛ ክፍል ትሰጣላችሁ፤ ዐሥር የባዶስ መስፈሪያ አንድ የቆሮስ መስፈሪያ ነውና። Ver Capítuloአዲሱ መደበኛ ትርጒም14 ዘይቱ በባዶስ ሲለካ፣ የተወሰነው መስፈሪያ ከእያንዳንዱ ሆሜር አንድ ዐሥረኛ ባዶስ ይሆናል፤ ይኸውም ዐሥር ባዶስ ወይም አንድ ሆሜር ነው፤ ዐሥር ባዶስ ከአንድ ሆሜር ጋራ እኩል ነውና። Ver Capítuloአማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም14 ከዘይትም የተመደበው ከያንዳንዱ ቆሮስ አንድ ዐሥረኛ ባት ነው። (አንድ ቆሮስ፥ አንድ ጎሞር ወይም ዐሥር ባት ማለት ነው) Ver Capítuloየአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)14 የዘይቱም ደንብ፥ ከእያንዳንዱ የቆሮስ መስፈሪያ የባዶስን ዐሥረኛ ክፍል ትሰጣላችሁ፤ ዐሥር የባዶስ መስፈሪያ አንድ የቆሮስ መስፈሪያ ነውና። Ver Capítuloመጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)14 የዘይቱም ደንብ፥ ከእያንዳንዱ የቆሮስ መስፈሪያ የባዶስን አሥረኛ ክፍል ትሰጣላችሁ፥ አሥር የባዶስ መስፈሪያ አንድ የቆሮስ መስፈሪያ ነውና። Ver Capítulo |