La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




ኢዮብ 37:16 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

የደ​መ​ና​ትን ክፍ​ሎች፥ አስ​ፈሪ የሆ​ነ​ው​ንም የኀ​ጢ​አ​ተ​ኞ​ችን አወ​ዳ​ደቅ ያው​ቃል።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

ደመናት ሚዛን ጠብቀው እንዴት እንደሚንሳፈፉ፣ በዕውቀቱ ፍጹም የሆነውን፣ የርሱን ድንቅ ሥራ ታውቃለህን?

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

ወይስ የደመናውን መንሳፈፍ፥ ወይስ በእውቀት ፍጹም የሆነውን ተአምራት አውቀሃልን?

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

ደመናን በሕዋው ላይ የሚያንሳፍፈውንና ሁሉን የሚያውቀውን የአምላክን ድንቅ ሥራ ታውቃለህን?

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

ወይስ የደመናውን ሚዛን፥ ወይስ በእውቀት ፍጹም የሆነውን ተአምራት አውቀሃልን?

Ver Capítulo



ኢዮብ 37:16
15 Referencias Cruzadas  

ውኃ​ውን በደ​መና ውስጥ ይቋ​ጥ​ራል፥ ደመ​ና​ውም ከታች አይ​ቀ​ደ​ድም።


አንድ ሰው የደ​መ​ና​ውን መዘ​ር​ጋት፥ ወይም የማ​ደ​ሪ​ያ​ውን ልክ ቢያ​ውቅ፥


ቃሌ ሐሰት ያይ​ደለ እው​ነት ነው። አን​ተም የዐ​መፅ ቃላ​ትን አት​ሰ​ማም።


“ኢዮብ ሆይ፥ ይህን ስማ፤ ቁም፥ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ኀይል ተገ​ሠጽ።


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሥራ​ውን እን​ዳ​ከ​ና​ወነ ከጨ​ለ​ማም ለይቶ ብር​ሃ​ንን እንደ ፈጠረ እና​ው​ቃ​ለን።


የአ​ዜብ ነፋስ በተ​ኮሰ ጊዜ ያንተ ልብ​ስህ የሞቀ ነው። እን​ግ​ዲህ በም​ድር ላይ ፀጥ በል።


ኀያሉ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በድ​ምፁ ድንቅ አድ​ርጎ ያን​ጐ​ደ​ጕ​ዳል፤ ለእ​ን​ስ​ሳት በየ​ጊ​ዜው ምግ​ባ​ቸ​ውን ያዘ​ጋ​ጃል፥ የሚ​ተ​ኙ​በ​ት​ንም ጊዜ ያው​ቃሉ፤ በዚህ ሁሉ ልብህ አይ​ደ​ን​ግ​ጥ​ብህ፤ ሥጋ​ህም ልብ​ህም ከግ​ዘፉ አይ​ለ​ወ​ጥ​ብህ፤ እር​ሱም እኛ የማ​ና​ው​ቀ​ውን ታላቅ ነገር ያደ​ር​ጋል።


እርሱ የማ​ይ​መ​ረ​መ​ረ​ውን ታላቅ ነገ​ርና የማ​ይ​ቈ​ጠ​ረ​ውን የከ​በ​ረና ድንቅ ነገር ያደ​ር​ጋል።


ሕዝ​ቡ​ንም እጅግ አበ​ዛ​ቸው፥ ከጠ​ላ​ቶ​ቻ​ቸ​ውም ይልቅ አበ​ረ​ታ​ቸው።


በረ​ዶ​ውን እንደ ባዘቶ ይሰ​ጣል፤ ጉሙን እንደ አመድ ይበ​ት​ነ​ዋል፤


ለጎ​ረ​ቤ​ቶ​ቻ​ች​ንም ስድብ ሆንን፥ በዙ​ሪ​ያ​ች​ንም ላሉ ሣቅና መዘ​በቻ።


እርሱ የም​ድ​ርን ክበብ ያጸ​ናል፤ በእ​ር​ስ​ዋም የሚ​ኖ​ሩት እንደ አን​በጣ ናቸው፤ ሰማ​ያ​ትን እንደ መጋ​ረጃ የሚ​ዘ​ረ​ጋ​ቸው፥ እንደ ድን​ኳ​ንም ለመ​ኖ​ሪያ የሚ​ዘ​ረ​ጋ​ቸው፤