ኢዮብ 30:25 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) ረዳት ለሌለው ሰው አለቀስሁ የተቸገረ ሰውን ባየሁ ጊዜ ጮኽሁ። አዲሱ መደበኛ ትርጒም በመከራ ውስጥ ላሉት አላለቀስሁምን? ለድኾችስ ነፍሴ አላዘነችምን? መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) ለተጨነቁት አላለቀስሁምን? ለችግረኛስ ነፍሴ አላዘነችምን? አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ለተቸገሩ ሰዎች አላለቀስኩምን? ለድኾችስ አልተጨነቅኹምን? መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) ጭንቅ ቀን ላገኘው ሰው አላለቀስሁምን? ለችግረኛስ ነፍሴ አላዘነችምን? |
ይህን ባትሰሙ ነፍሴ ስለ ትዕቢታችሁ በስውር ታለቅሳለች፤ የእግዚአብሔርም መንጋ ተሰብሮአልና ዐይኔ ታነባለች፤ እንባንም ታፈስሳለች።
ለሰውነቴ ጕድጓድን ቈፍረዋል፤ በውኑ በመልካም ፈንታ ክፉ ይመለሳልን? ስለ እነርሱ በመልካም እናገር ዘንድ፥ ቍጣህንም ከእነርሱ ትመልስ ዘንድ በፊትህ እንደ ቆምሁ አስብ።