La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




ሕዝቅኤል 40:3 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

ወደ​ዚ​ያም አመ​ጣኝ፤ እነ​ሆም መልኩ እን​ደ​ሚ​ያ​ን​ፀ​ባ​ርቅ ናስ መልክ የመ​ሰለ አንድ ሰው በዚያ ነበረ፤ በእ​ጁም የተ​ልባ እግር ገመ​ድና የመ​ለ​ኪያ ዘንግ ነበረ፤ እር​ሱም በበሩ አጠ​ገብ ቆሞ ነበር።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

ወደዚያ ወሰደኝ፤ እነሆ መልኩ ናስ የሚመስል ሰው አየሁ፤ እርሱም የሐር ገመድና መለኪያ ዘንግ በእጁ ይዞ በመግቢያው በር ላይ ቆሞ ነበር።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

ወደዚያም አመጣኝ፥ እነሆ፥ መልኩ ናስ የመሰለ አንድ ሰው በዚያ ነበረ፥ በእጁም የተልባ እግር ገመድና የመለኪያ ዘንግ ይዞ ነበረ፤ እርሱም በበሩ አጠገብ ቆሞ ነበር።

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

ወደዚያ ሲወስደኝም እንደ ነሐስ የሚያበራ መልክ ያለውን አንድ ሰው አየሁ፤ እርሱም ከበፍታ የተሠራ ገመድና መለኪያ ዘንግ ይዞ በቅጽሩ በር አጠገብ ቆሞ ነበር።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

ወደዚያም አመጣኝ፥ እነሆም፥ መልኩ እንደ ናስ መልክ የመሰለ አንድ ሰው በዚያ ነበረ፥ በእጁም የተልባ እግር ገመድና የመለኪያ ዘንግ ነበረ፥ እርሱም በበሩ አጠገብ ቆሞ ነበር።

Ver Capítulo



ሕዝቅኤል 40:3
14 Referencias Cruzadas  

ፍር​ዴን ለተ​ስፋ ይቅ​ር​ታ​ዬ​ንም ለት​ክ​ክ​ለኛ ሚዛን አደ​ር​ጋ​ለሁ፤ በከ​ን​ቱና በሐ​ሰት የሚ​ታ​መኑ ከዐ​ውሎ ነፋስ አያ​መ​ል​ጡም።


ነገሩ እን​ዲህ አይ​ደ​ለም ይሉ ዘንድ፥ ለእ​ር​ሱም ግብር እን​ዳ​ይ​ሰጡ ሕግን ለር​ዳታ ሰጥ​ቶ​አ​ልና።


ከወ​ገ​ቡም አም​ሳያ ወደ ላይ የሚ​ብ​ለ​ጨ​ለጭ የወ​ርቅ አም​ሳያ አየሁ፤ ከወ​ገ​ቡም አም​ሳያ ወደ ታች እንደ እሳት አም​ሳያ አየሁ፤ በዙ​ሪ​ያ​ውም ፀዳል ነበረ።


እግ​ሮ​ቻ​ቸ​ውም ቀጥ ያሉ ነበሩ፤ የእ​ግ​ራ​ቸው ሰኰና እንደ ላም እግር ሰኰና ነበረ፤ እንደ ተወ​ለ​ወለ ናስም ይብ​ለ​ጨ​ለጭ ነበር።


ወደ መቅ​ደ​ሱም አገ​ባኝ፤ የግ​ን​ቡ​ንም አዕ​ማድ ወርድ በዚህ ወገን ስድ​ስት ክንድ፥ በዚ​ያም ወገን ስድ​ስት ክንድ አድ​ርጎ ለካ።


ወደ ምሥ​ራቅ በሚ​መ​ለ​ከ​ተ​ውም በር ኋላ ቆመ፤ የም​ሥ​ራ​ቁን ወገን በመ​ለ​ኪያ ዘንግ አም​ስት መቶ ክንድ አድ​ርጎ ለካ።


በመ​ቅ​ደ​ሱም ሆኖ የሚ​ና​ገ​ረ​ኝን ሰማሁ፤ በአ​ጠ​ገ​ቤም ሰው ቆሞ ነበር።


ሰው​ዮ​ውም የመ​ለ​ኪያ ገመድ በእጁ ይዞ ወደ ምሥ​ራቅ ወጣ፤ አንድ ሺህም ክንድ ለካ፤ በው​ኃ​ውም ውስጥ አሻ​ገ​ረኝ፤ ውኃ​ውም እስከ ቍር​ጭ​ም​ጭ​ሚት ደረሰ።


እኔም አየሁ፤ እነ​ሆም ከወ​ገቡ በታች እንደ እሳት የሚ​መ​ስል የሰው አም​ሳያ ነበረ፤ ከወ​ገ​ቡም ወደ ላይ እንደ ፀዳል ምሳሌ፥ እን​ደ​ሚ​ያ​ን​ጸ​ባ​ርቅ አይ​ነት ነበረ።


እግሮቹም በእቶን የነጠረ የጋለ ናስ ይመስሉ ነበር፤ ድምፁም እንደ ብዙ ውሃዎች ድምፅ ነበረ።


በትር የሚመስል መለኪያ ለእኔ ተሰጠኝ፤ እንዲህም ተባልሁ “ተነሥተህ የእግዚአብሔርን መቅደስና መሠዊያውን በዚያም የሚሰግዱትን ለካ።


የተናገረኝም ከተማይቱንና ደጆችዋን ቅጥርዋንም ይለካ ዘንድ የወርቅ ዘንግ ነበረው።