ዘፀአት 36:21 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) የሳንቃው ሁሉ ርዝመቱ ዐሥር ክንድ፥ ወርዱም አንድ ክንድ ተኩል ነበረ። አዲሱ መደበኛ ትርጒም እያንዳንዱም ወጋግራ ቁመቱ ዐሥር ክንድ፣ ስፋቱ አንድ ክንድ ተኩል ነበር፤ መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) የእያንዳንዱ ሳንቃ ርዝመት ዐሥር ክንድ፥ ወርድ አንድ ክንድ ተኩል ነበረ። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም እያንዳንዱ ተራዳ ቁመቱ አራት ሜትር የጐኑም ስፋት ሥልሳ ስድስት ሳንቲ ሜትር ሲሆን፥ መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) የሳንቃው ሁሉ ርዝመቱ አሥር ክንድ፥ ወርዱም አንድ ክንድ ተኩል ነበረ። |
ለእያንዳንዱም ሳንቃ አንዱን በአንዱ ላይ የሚያያይዙ ሁለት ማጋጠሚያዎች ነበሩ፤ ለድንኳኑም ሳንቆች ሁሉ እንዲሁ አደረጉ።