La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




2 ዜና መዋዕል 28:27 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

አካ​ዝም ከአ​ባ​ቶቹ ጋር አን​ቀ​ላፋ፤ በዳ​ዊ​ትም ከተማ ቀበ​ሩት፤ ነገር ግን ወደ እስ​ራ​ኤል ነገ​ሥ​ታት መቃ​ብር አላ​ገ​ቡ​ትም፤ ልጁም ሕዝ​ቅ​ያስ በእ​ርሱ ፋንታ ነገሠ።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

አካዝ ከአባቶቹ ጋራ አንቀላፋ፤ በኢየሩሳሌምም ከተማ ተቀበረ፤ የተቀበረው ግን በእስራኤል ነገሥታት መካነ መቃብር አልነበረም። ልጁ ሕዝቅያስም በምትኩ ነገሠ።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

አካዝም ከአባቶቹ ጋር አንቀላፋ፥ በከተማይቱም በኢየሩሳሌም ቀበሩት፤ ነገር ግን ወደ እስራኤል ነገሥታት መቃብር አላገቡትም፤ ልጁም ሕዝቅያስ በእርሱ ፋንታ ነገሠ።

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

ንጉሥ አካዝ ሞተ፤ በኢየሩሳሌምም ተቀበረ፤ ይሁን እንጂ በነገሥታት መካነ መቃብር አልተቀበረም፤ በእርሱም እግር ተተክቶ ልጁ ሕዝቅያስ ነገሠ።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

አካዝም ከአባቶቹ ጋር አንቀላፋ፤ በከተማይቱም በኢየሩሳሌም ቀበሩት፤ ነገር ግን ወደ እስራኤል ነገሥታት መቃብር አላገቡትም፤ ልጁም ሕዝቅያስ በእርሱ ፋንታ ነገሠ።

Ver Capítulo



2 ዜና መዋዕል 28:27
11 Referencias Cruzadas  

አካ​ዝም እንደ አባ​ቶቹ አን​ቀ​ላፋ፥ በዳ​ዊ​ትም ከተማ ተቀ​በረ፤ ልጁም ሕዝ​ቅ​ያስ በእ​ርሱ ፋንታ ነገሠ።


እን​ዲ​ህም ሆነ፤ የእ​ስ​ራ​ኤል ንጉሥ የኤላ ልጅ ሆሴዕ በነ​ገሠ በሦ​ስ​ተ​ኛው ዓመት የይ​ሁዳ ንጉሥ የአ​ካዝ ልጅ ሕዝ​ቅ​ያስ ነገሠ።


ለእ​ር​ሱም የኢ​ዮ​ሣ​ፍጥ ልጆች አዛ​ር​ያስ፥ ኢይ​ሔል፥ ዘካ​ር​ያስ፥ ዔዛ​ር​ያስ፥ ሚካ​ኤል፥ ሰፋ​ጥ​ያስ የሚ​ባሉ ስድ​ስት ወን​ድ​ሞች ነበ​ሩት፤ እነ​ዚህ ሁሉ የይ​ሁዳ ንጉሥ የኢ​ዮ​ሣ​ፍጥ ልጆች ነበሩ።


መን​ገ​ሥም በጀ​መረ ጊዜ የሠ​ላሳ ሁለት ዓመት ጐል​ማሳ ነበረ፤ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም ስም​ንት ዓመት ነገሠ፤ ማንም ሳያ​ዝ​ን​ለት ሄደ፤ በዳ​ዊ​ትም ከተማ እንጂ በነ​ገ​ሥ​ታት መቃ​ብር አል​ቀ​በ​ሩ​ትም።


ከእ​ር​ሱም ዘንድ አል​ፈው ከሄዱ በኋላ እጅግ ታሞ ሳለ ተዉት፤ የገዛ ባሪ​ያ​ዎ​ቹም ስለ ካህኑ ስለ ኢዮ​አዳ ልጅ ደም ተበ​ቅ​ለው በአ​ል​ጋው ላይ ገደ​ሉት፤ ሞተም፤ በዳ​ዊ​ትም ከተማ ቀበ​ሩት፤ ነገር ግን በነ​ገ​ሥ​ታት መቃ​ብር አል​ቀ​በ​ሩ​ትም።


ዖዝ​ያ​ንም ከአ​ባ​ቶቹ ጋር አን​ቀ​ላፋ፤ ለም​ጻም ነው ብለ​ዋ​ልና የነ​ገ​ሥ​ታቱ መቃ​ብር ባል​ሆነ እርሻ ውስጥ ቀበ​ሩት፤ ልጁም ኢዮ​አ​ታም በእ​ርሱ ፋንታ ነገሠ።


ሕዝ​ቅ​ያ​ስም የሃያ አም​ስት ዓመት ጐል​ማሳ በነ​በረ ጊዜ መን​ገሥ ጀመረ፤ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም ሃያ ዘጠኝ ዓመት ነገሠ፤ እና​ቱም የዘ​ካ​ር​ያስ ልጅ አብያ ትባል ነበር።


ቍጥሩ ከባ​ሕር አሸዋ የሚ​በ​ልጥ በደ​ልን በድ​ያ​ለ​ሁና፥ ኀጢ​አ​ቴም ብዙ ነውና፤ ከበ​ደ​ሌም ብዛት የተ​ነሣ ቀና ብዬ የሰ​ማ​ይን ርዝ​መት አይ ዘንድ አገ​ባቤ አይ​ደ​ለም። ሰው​ነ​ቴን ከኀ​ጢ​አቴ አሳ​ር​ፋት ዘንድ በብ​ረት ቀፎ ደከ​ምሁ፤ በዚ​ህም ደግሞ አላ​ረ​ፍ​ሁም፤ መዓ​ት​ህን አነ​ሣ​ሥ​ቻ​ለ​ሁና፥


የጻድቃን መታሰቢያ ከምስጋና ጋር ነው። የኃጥኣን ስም ግን ይጠፋል።


ንጉሡ አካዝ በሞ​ተ​በት ዓመት ይህ ነገር ሆነ።


ስለ​ዚ​ህም የእ​ስ​ራ​ኤል አም​ላክ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፦ በእ​ው​ነት ቤትህ፥ የአ​ባ​ት​ህም ቤት፤ ለዘ​ለ​ዓ​ለም በፊቴ እን​ዲ​ኖር ተና​ግ​ሬ​አ​ለሁ፤ አሁን ግን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፦ ያከ​በ​ሩ​ኝን አከ​ብ​ራ​ለ​ሁና፥ የና​ቁ​ኝም ይና​ቃ​ሉና ይህ አይ​ሆ​ን​ል​ኝም።