ክብራቸው የሆነውንም ሣር በሚበላ፣ በበሬ ምስል ለወጡ።
ሣርም በሚበላ በበሬ ምሳሌ ክብራቸውን ለወጡ።
የእግዚአብሔርንም ክብር ሣር በሚበላ እንስሳ ምስል ለወጡ።
ቃሉን ልኮ ፈወሳቸው፥ ከጥፋታቸውም አዳናቸው።
አንተ የብርታታቸው ክብር ነህና፤ በሞገስህም ቀንዳችንን ከፍ ከፍ አደረግህ።
እርሱም የሰጡትን ወስዶ በመሣሪያ በመቅረጽ በጥጃ ምስል ጣዖት አድርጎ ሠራው፤ ከዚያም እነርሱ፣ “እስራኤል ሆይ፤ ከግብጽ ያወጡህ አማልክት እነዚህ ናቸው” አሉ።
የእውነት አማልክት ባይሆኑም እንኳ፣ አማልክቱን የለወጠ ሕዝብ አለን? ሕዝቤ ግን ክብራቸው የሆነውን፣ በከንቱ ነገር ለወጡ።