እርሱም ወዲያው ከለምጹ ነጻ፤ ከበሽታውም ተፈወሰ።
ሰውየውም ወዲያውኑ ከለምጹ ነጻ።
በተናገረም ጊዜ ለምጹ ወዲያው ለቀቀውና ነጻ።
እርሱ ተናግሯልና ሆኑ፤ አዝዟልና ጸኑም።
በዚህ ጊዜ ኢየሱስ፣ “አንቺ ሴት እምነትሽ ታላቅ ነው! እንደ ፈለግሽው ይሁንልሽ” አላት። ልጇም ከዚያ ሰዓት ጀምሮ ተፈወሰች።
ስለዚህም እርሱ ወደ ተኛችበት በመሄድ እጇን ይዞ አስነሣት፤ ትኵሳቱም ተዋት፤ ተነሥታም ታገለግላቸው ጀመር።
ኢየሱስም ለሰውየው በመራራት እጁን ዘርግቶ ዳሰሰውና፣ “እፈቅዳለሁ፣ ንጻ!” አለው።
ኢየሱስም ሰውየውን አጥብቆ በማስጠንቀቅ እንዲህ ሲል አሰናበተው፤
የሚፈስሰው ደሟም ወዲያውኑ ቆመ፤ ከሥቃይዋ መገላገሏም በሰውነቷ ታወቃት።
ከነገርኋችሁ ቃል የተነሣ እናንተ አሁን ንጹሓን ናችሁ።