La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




ኢዮብ 10:15 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

በደ​ለኛ ብሆን ወዮ​ልኝ፤ ጻድ​ቅም ብሆን ራሴን አላ​ነ​ሣም፤ ጕስ​ቍ​ል​ና​ንም ጠገ​ብ​ኋት።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

በደለኛ ብሆን ወዮልኝ፤ ንጹሕ ብሆንም፣ ራሴን ቀና አላደርግም፤ ውርደትን ተከናንቤአለሁና፤ በመከራም ተዘፍቄአለሁ።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

በደለኛ ብሆን ወዮልኝ፥ ጻድቅም ብሆን ራሴን አላነሣም፥ ጉስቁልናን ተሞልቻለሁና፥ መከራዬንም ተመልክቻለሁና።

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

ኃጢአት ብሠራ ወዲያው ችግር ውስጥ እወድቃለሁ ደግ ነገር ብሠራም አልመሰገንም ተጐሣቊዬ ኀፍረት ደርሶብኛል።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

በደለኛ ብሆን ወዮልኝ፥ ጻድቅም ብሆን ራሴን አላነሣም፥ ጕስቍልናን ተሞልቻለሁ፥ መከራዬንም ተመልክቻለሁ።

Ver Capítulo



ኢዮብ 10:15
23 Referencias Cruzadas  

ከዚህ በላይ በደ​ለኛ እን​ዳ​ል​ሆ​ንሁ፥ አንተ ታው​ቃ​ለህ። ነግር ግን ከእ​ጅህ የሚ​ያ​መ​ልጥ ማን ነው?


እኔ ባሰ​ብሁ ቍጥር እጨ​ነ​ቃ​ለሁ፤ ጻዕ​ርም ሥጋ​ዬን ይይ​ዛል።


ስለ​ዚህ በፊቱ ደነ​ገ​ጥሁ፤ አስ​በ​ዋ​ለሁ፤ ከእ​ር​ሱም የተ​ነሣ እፈ​ራ​ለሁ።


ጠላ​ቶች እንደ ኀጢ​አ​ተ​ኞች ውድ​ቀት፥ በእኔ ላይም የሚ​ነሡ እንደ በደ​ለ​ኞች ጥፋት ይሁኑ።


አሁ​ንም ተቀ​መጡ፤ በደ​ልም አይ​ኑር፤ ዳግ​መ​ኛም ከጻ​ድቁ ጋር አንድ ሁኑ።


እርሱ ቢያ​ርቅ የሚ​መ​ልስ ማን ነው? እር​ሱ​ንስ፦ ምን ታደ​ር​ጋ​ለህ? የሚ​ለው ማን ነው?


በጽ​ድቅ ብጠ​ራው፥ ባይ​ሰ​ማ​ኝም፥ የእ​ር​ሱን ፍርድ እለ​ም​ና​ለሁ።


“ኃጢ​ኣ​ተኛ ሰው ከሆ​ንሁ፤ ስለ ምን አል​ሞ​ት​ሁም?


በአ​ባ​ቶ​ችሽ ፋንታ ልጆች ተወ​ለ​ዱ​ልሽ፥ በም​ድ​ርም ሁሉ ላይ ገዥ​ዎች አድ​ር​ገሽ ትሾ​ሚ​ያ​ቸ​ዋ​ለሽ።


ኀጢ​አ​ተ​ኞች ወደ ሲኦል ይመ​ለሱ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የሚ​ረሱ አሕ​ዛ​ብም ሁሉ።


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ሙሴን አለው፥ “በግ​ብፅ ያለ​ውን የሕ​ዝ​ቤን መከራ በእ​ው​ነት አየሁ፦ ከአ​ሠ​ሪ​ዎ​ቻ​ቸ​ውም የተ​ነሣ ጩኸ​ታ​ቸ​ውን ሰማሁ፤ ሥቃ​ያ​ቸ​ው​ንም ዐው​ቄ​አ​ለሁ፤


እንደ እጁ ሥራ ፍዳው ይደ​ረ​ግ​በ​ታ​ልና ለበ​ደ​ለኛ ወዮ! ክፉም ይደ​ር​ስ​በ​ታል።


እኔም፥ “ከን​ፈ​ሮች የረ​ከ​ሱ​ብኝ ሰው በመ​ሆኔ፥ ከን​ፈ​ሮ​ቻ​ቸው በረ​ከ​ሱ​ባ​ቸው ሕዝብ መካ​ከል በመ​ቀ​መጤ ዐይ​ኖች የሠ​ራ​ዊ​ትን ጌታ ንጉ​ሡን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ስለ አዩ ጠፍ​ቻ​ለ​ሁና ወዮ​ልኝ!” አልሁ።


ሬስ። አቤቱ! ተጨ​ን​ቄ​አ​ለ​ሁና፥ አን​ጀ​ቴም ታው​ኮ​ብ​ኛ​ልና ተመ​ል​ከት፤ መራራ ኀዘን አዝ​ኛ​ለ​ሁና ልቤ በው​ስጤ ተገ​ላ​በ​ጠ​ብኝ፤ በሜዳ ሰይፍ አመ​ከ​ነ​ችኝ፤ በቤ​ትም ሞት አለ።


ተመልሳችሁም በጻድቁና በኃጢአተኛው መካከል፥ ለእግዚአብሔር በሚገዛውና በማይገዛው መካከል ትለያላችሁ።


እን​ዲሁ እና​ን​ተም ያዘ​ዝ​ኋ​ች​ሁን ሁሉ አድ​ር​ጋ​ችሁ ‘እኛ ሥራ ፈቶች አገ​ል​ጋ​ዮች ነን፤ ለመ​ሥ​ራ​ትም የሚ​ገ​ባ​ንን ሠራን’ በሉ።”