የጓዳዎቹም መግቢያ ብቻውን ወደሚኖረው ስፍራ ነበረ፤ አንዱ ደጅ ወደ ሰሜን መንገድ፤ አንዱም ደጅ ወደ ደቡብ መንገድ፥ ብቻውን የሚኖረው ስፍራ ወርዱ አምስት ክንድ በዙሪያው ነበር።
ሕዝቅኤል 41:9 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) የጓዳዎቹም የውጭው ግንብ ወርድ አምስት ክንድ ነበረ፤ በመቅደሱም ጓዳዎች አጠገብ የቀረ አንድ ባዶ ስፍራ ነበረ። አዲሱ መደበኛ ትርጒም በውጭ በኩል ያለው የግራና የቀኙ ክፍሎች ግንብ ውፍረት ዐምስት ክንድ ነበር፤ ክፍቱ ቦታ በቤተ መቅደሱና መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) የጓዳዎቹም የውጭው ግንብ ውፍረት አምስት ክንድ ነበረ፤ በቤቱ ጓዳዎች አጠገብ የቀረ ባዶ ስፍራ ነበረ። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም የውጪው ክፍሎች ግድግዳ ውፍረት አምስት ክንድ ነበር፤ ከቤተ መቅደሱ ጐን ካሉት ክፍሎችና ከሚቀጥሉት ሕንጻዎች መካከል ባዶ ቦታ ነበር፤ የዚህም ባዶ ቦታ ስፋት በሃያ ክንድ ቤተ መቅደሱን ይዞር ነበር። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) የጓዳዎቹም የውጭው ግንብ ውፍረት አምስት ክንድ ነበረ፥ በመቅደሱም ጓዳዎች አጠገብ የቀረ አንድ ባዶ ስፍራ ነበረ። |
የጓዳዎቹም መግቢያ ብቻውን ወደሚኖረው ስፍራ ነበረ፤ አንዱ ደጅ ወደ ሰሜን መንገድ፤ አንዱም ደጅ ወደ ደቡብ መንገድ፥ ብቻውን የሚኖረው ስፍራ ወርዱ አምስት ክንድ በዙሪያው ነበር።
በውጭም አደባባይ በሰሜኑ መንገድ በምሥራቅ በኩል አወጣኝ፤ በልዩውም ስፍራ አንጻርና በሰሜን በኩል በአለው ግቢ ፊት ለፊት ወዳሉት አምስት ዕቃ ቤቶች አገባኝ።
በዕቃ ቤቶቹም ፊት በስተውስጥ ወርዱ ዐሥር ክንድ፥ ርዝመቱ መቶ ክንድ የሆነ መንገድ ነበረ፤ መግቢያዎቻቸውም ወደ ሰሜን ይመለከቱ ነበር።