La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




ሕዝቅኤል 38:2 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

“የሰው ልጅ ሆይ! ፊት​ህን በጎግ ላይና በማ​ጎግ ምድር ላይ፥ በሮስ በሞ​ሳ​ሕና በቶ​ቤል አለቃ ላይ አቅ​ና​በት፤ ትን​ቢ​ትም ተና​ገ​ር​በት፤

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

“የሰው ልጅ ሆይ፤ ፊትህን በማጎግ ምድር በሚገኘው፣ በሜሼኽና በቶቤል ዋና አለቃ በጎግ ላይ አድርግ፤ በርሱ ላይ ትንቢት ተናገር፤

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

የሰው ልጅ ሆይ፥ የማጎግ ምድር፥ በሮሽ፥ በሜሼኽና በቱባል ላይ አለቃ ወደ ሆነው ወደ ጎግ ፊትህን አቅና፥ ትንቢትም ተናገርበት፥

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

“የሰው ልጅ ሆይ! በማጎግ ምድር የሚገኙት የሜሼክና የቱባል ሕዝቦች ገዢ የሆነውን ጎግን በመቃወም ትንቢት ተናገርበት፤

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

የሰው ልጅ ሆይ፥ ፊትህን በጎግ ላይና በማጎግ ምድር ላይ፥ በሞሳሕና በቶቤል ዋነኛ አለቃ ላይ አቅናበት፥ ትንቢትም ተናገርበት፥

Ver Capítulo



ሕዝቅኤል 38:2
18 Referencias Cruzadas  

የያ​ፌት ልጆች ጋሜር፥ ማጎግ፥ ማዴ፥ ይህ​ያን፥ ይልሳ፥ ቶቤል፥ሞሳሕ፥ ቴራስ ናቸው።


የያ​ፌት ልጆች ጋሜር፥ ማጎግ፥ ማዳይ፥ ይሕ​ያን፥ ኤልሳ፥ ቶቤል፥ ሞሳ​ሕና ቲራም።


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይጠ​ብ​ቅህ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በቀኝ እጁ ይጋ​ር​ድህ።


በመ​ካ​ከ​ላ​ቸ​ውም ምል​ክት አደ​ር​ጋ​ለሁ፤ ከእ​ነ​ር​ሱም ከሞት የዳ​ኑ​ትን ዝና​ዬን ወዳ​ል​ሰሙ፥ ክብ​ሬ​ንም ወዳ​ላዩ ወደ አሕ​ዛብ ወደ ተር​ሴስ፥ ወደ ፉጥ፥ ወደ ሉድ፥ ወደ ሞሳሕ፥ ወደ ቶቤል፥ ወደ ኤላድ በሩቅ ወዳሉ ደሴ​ቶች እል​ካ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ በአ​ሕ​ዛ​ብም መካ​ከል ክብ​ሬን ይና​ገ​ራሉ።


እር​ሱም፥ “የሰው ልጅ ሆይ! በእ​ግ​ርህ ቁም፤ እኔም እና​ገ​ር​ሃ​ለሁ” አለኝ።


“የሰው ልጅ ሆይ! ፊት​ህን ወደ ቴማን አቅና፤ ወደ ዳሮ​ምም ተመ​ል​ከት፤ በና​ጌ​ብም ምድረ በዳ ዱር ንጉሥ ላይ ትን​ቢት ተና​ገር።


“የሰው ልጅ ሆይ! ፊት​ህን ወደ አሞን ልጆች አቅ​ን​ተህ ትን​ቢት ተና​ገ​ር​ባ​ቸው።


ያዋ​ንና ቶቤል፥ ሞሳ​ሕም ነጋ​ዴ​ዎ​ችሽ ነበሩ፤ ንግ​ድ​ሽ​ንም በሰ​ዎች ነፍ​ሳ​ትና በናስ ዕቃ አደ​ረጉ።


“ሞሳ​ሕና ቶቤል፥ ሠራ​ዊ​ታ​ቸ​ውም ሁሉ በዚያ አሉ፤ መቃ​ብ​ራ​ቸ​ውም በዙ​ሪ​ያ​ቸው ነው፤ ሁሉም ሳይ​ገ​ረዙ በሰ​ይፍ ተገ​ድ​ለ​ዋል፤ በሕ​ያ​ዋን ምድር ያስ​ፈሩ ነበ​ርና።


የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ቃል ወደ እኔ እን​ዲህ ሲል መጣ፦


አንተ የሰው ልጅ ሆይ! ስለ​ዚህ ትን​ቢት ተና​ገር፤ ጎግ​ንም እን​ዲህ በለው፥ “ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፦ በዚያ ቀን ሕዝቤ እስ​ራ​ኤል በሰ​ላም በተ​ቀ​መጠ ጊዜ አንተ የም​ት​ነሣ አይ​ደ​ለ​ምን?


እን​ዲ​ህም በል፦ ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፦ የሮስ፥ የሞ​ሣ​ሕና የቶ​ቤል አለቃ ጎግ ሆይ! እነሆ! እኔ በአ​ንተ ላይ ነኝ።


“አን​ተም የሰው ልጅ ሆይ! በጎግ ላይ ትን​ቢ​ትን ተና​ገር እን​ዲ​ህም በል፦ ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፦ የሮስ የሞ​ሣ​ሕና የቶ​ቤል አለቃ ጎግ ሆይ! እነሆ እኔ በአ​ንተ ላይ ነኝ፤


“በዚ​ያም ቀን በእ​ስ​ራ​ኤል ዘንድ በባ​ሕር ምሥ​ራቅ የሚ​ያ​ል​ፉ​በ​ትን ሸለቆ፥ የመ​ቃ​ብ​ርን ስፍራ ለጎግ እሰ​ጣ​ለሁ፤ የሚ​ያ​ል​ፉ​ት​ንም ይከ​ለ​ክ​ላል፤ በዚ​ያም ጎግ​ንና ሠራ​ዊ​ቱን ሁሉ ይቀ​ብ​ራሉ፤ የሸ​ለ​ቆ​ው​ንም ስም የጎግ መቃ​ብር ብለው ይጠ​ሩ​ታል።


በማ​ጎ​ግም ላይ፥ በሰ​ላ​ምም በደ​ሴ​ቶች በሚ​ቀ​መጡ ላይ እሳ​ትን እሰ​ድ​ዳ​ለሁ፤ እኔም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሆንሁ ያው​ቃሉ።


“የሰው ልጅ ሆይ፥ ፊት​ህን ወደ እስ​ራ​ኤል ተራ​ሮች አቅና፤ ትን​ቢ​ትም ተና​ገ​ር​ባ​ቸው።