La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




ሕዝቅኤል 1:11 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

ክን​ፋ​ቸ​ውም በላይ ተዘ​ር​ግቶ ነበር፤ የእ​ያ​ን​ዳ​ን​ዱም ሁለት ሁለት ክን​ፋ​ቸው የተ​ያ​ያዙ ነበሩ፤ ሁለት ሁለ​ቱም ገላ​ቸ​ውን ይከ​ድኑ ነበር።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

እንግዲህ ፊታቸው ይህን ይመስል ነበር፤ ክንፋቸውም ወደ ላይ ተዘርግቶ ነበር፤ እያንዳንዳቸው ሁለት ሁለት ክንፍ ነበራቸው፤ የእያንዳንዱም ክንፍ የሌላውን ክንፍ ይነካ ነበር፤ ሁለቱ ክንፎቻቸው ሰውነታቸውን ይሸፍኑ ነበር።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

ፊታቸው እንዲህ ነበረ። ክንፎቻቸውም ወደ ላይ ተዘርግተው ነበር፥ የእያንዳንዳቸውም ሁለት ክንፋቸው የተያያዙ ነበሩ፥ በሁለቱም ገላቸውን ይከድኑ ነበር።

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

የእያንዳንዱ እንስሳ ሁለት ክንፎች ወደ ላይ ከፍ ብለው ከእነርሱ ቀጥሎ ያለውን ፍጥረት የክንፎች ጫፍ ይነኩ ነበር፤ የቀሩት ሁለቱ ክንፎቻቸው ግን ተጣጥፈው አካላቸውን ይሸፍኑ ነበር።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

ክንፋቸውም በላይ ተዘርግቶ ነበር፥ የእያንዳንዱም ሁለት ሁለት ክንፋቸው የተያያዙ ነበሩ፥ ሁለት ሁለቱም ገላቸውን ይከድኑ ነበር።

Ver Capítulo



ሕዝቅኤል 1:11
4 Referencias Cruzadas  

ሱራ​ፌ​ልም በዙ​ሪ​ያው ቆመው ነበር፤ ለእ​ያ​ን​ዳ​ን​ዱም ስድ​ስት ክንፍ ነበ​ረው፤ በሁ​ለቱ ክን​ፎ​ቻ​ቸው ፊታ​ቸ​ውን ይሸ​ፍኑ ነበር፤ በሁ​ለ​ቱም ክን​ፎ​ቻ​ቸው እግ​ሮ​ቻ​ቸ​ውን ይሸ​ፍኑ ነበር፤ በሁ​ለ​ቱም ክን​ፎ​ቻ​ቸው ይበ​ርሩ ነበር።


ከጠ​ፈ​ሩም በታች ክን​ፎ​ቻ​ቸው እርስ በር​ሳ​ቸው ተቃ​ን​ተው ነበር፤ ለእ​ያ​ን​ዳ​ን​ዱም ገላ​ውን የሚ​ከ​ድኑ ሁለት ሁለት ክን​ፎች ነበ​ሩት።


ኪሩ​ቤ​ልም ሲሄዱ መን​ኰ​ራ​ኵ​ሮቹ ከእ​ነ​ርሱ ጋር ተያ​ይ​ዘው ይሄዱ ነበር፤ ኪሩ​ቤ​ልም ይበሩ ዘንድ ክን​ፋ​ቸ​ውን ከም​ድር በሚ​ያ​ነሡ ጊዜ ከእ​ነ​ርሱ ጋር የተ​ያ​ያዘ መን​ኰ​ራ​ኵ​ራ​ቸው አይ​መ​ለ​ስም ነበር።


ኪሩ​ቤ​ልም ክን​ፎ​ቻ​ቸ​ውን ዘረጉ፤ እኔም እያ​የሁ ከም​ድር በረሩ፤ በወ​ጡም ጊዜ መን​ኰ​ራ​ኵ​ሮቹ በአ​ጠ​ገ​ባ​ቸው ነበሩ፤ፊት ለፊት በአ​ለው በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት መግ​ቢያ በር ዳርቻ ቆሙ፤ የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም አም​ላክ ክብር ከእ​ነ​ርሱ ጋራ በላ​ያ​ቸው ነበረ።