La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




2 ዜና መዋዕል 34:12 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

ሰዎ​ቹም ሥራ​ውን በመ​ታ​መን አደ​ረጉ፤ በእ​ነ​ር​ሱም ላይ የተ​ሾ​ሙት፥ ሥራ​ው​ንም የሚ​ያ​ሠ​ሩት ሌዋ​ው​ያን ከሜ​ራሪ ልጆች ይኤ​ትና አብ​ድ​ያስ፥ ከቀ​ዓ​ትም ልጆች ዘካ​ር​ያ​ስና ሜሱ​ላም ነበሩ። ከሌ​ዋ​ው​ያ​ንም ወገን በዜማ ዕቃ ዐዋ​ቂ​ዎች፥ የነ​በሩ ሁሉ፥

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

ሰዎቹም ሥራውን በታማኝነት አከናወኑ። የበላይ ሆነው አመራር የሚሰጧቸውም ከሜራሪ ጐሣ የሆኑት ሌዋውያን፣ ኢኤትና አብድዩ፣ ከቀዓት ጐሣ ዘካርያስና ሜሱላም ነበሩ። በዜማ ዕቃ የላቀ ችሎታ የነበራቸው ሌዋውያን ሁሉ፣

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

ሰዎቹም ሥራውን በታማኝነት ሠሩ፤ በእነርሱም ላይ የተሾሙት፥ ሥራውንም የሚሠሩት ሌዋውያን ከሜራሪ ልጆች ኢኤትና አብድዩ፥ ከቀዓትም ልጆች ዘካርያስና ሜሱላም ነበሩ። ከሌዋውያንም ወገን በዜማ ዕቃ አዋቂዎች የነበሩ ሁሉ

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

አናጢዎቹና ግንበኞቹም ሥራውን በታማኝነት አከናወኑ፤ የእነርሱም የበላይ ተቈጣጣሪዎች ከመራሪ ጐሣ ያሐትና አብድዩ፥ ከቀዓት ጐሣ ዘካርያስና መሹላም ተብለው የሚጠሩት አራት ሌዋውያን ነበሩ፤ (ሌዋውያን ሁሉ በዜማ መሣሪያ የመዘመር ከፍ ያለ ችሎታ ያላቸው ሰዎች ነበሩ፤)

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

ሰዎቹም ሥራውን በመታመን አደረጉ፤ በእነርሱም ላይ የተሾሙት፥ ሥራውንም የሚሠሩት ሌዋውያን ከሜራሪ ልጆች ኢኤትና አብድዩ፥ ከቀዓትም ልጆች ዘካርያስና ሜሱላም ነበሩ። ከሌዋውያንም ወገን በዜማ ዕቃ አዋቂዎች የነበሩ ሁሉ

Ver Capítulo



2 ዜና መዋዕል 34:12
15 Referencias Cruzadas  

የሌ​ዊም ልጆች፤ ጌድ​ሶን፥ ቀዓት፥ ሜራሪ።


ለሠ​ራ​ተ​ኞ​ችም ይከ​ፍሉ ዘንድ ገን​ዘ​ቡን የሚ​ወ​ስ​ዱ​ትን ሰዎች አይ​ቈ​ጣ​ጠ​ሩ​አ​ቸ​ውም ነበር፤ በታ​ማ​ኝ​ነት ይሠሩ ነበ​ርና።


ነገር ግን እነ​ርሱ በእ​ም​ነት ይሠሩ ነበ​ርና የሰ​ጡ​አ​ቸ​ውን ገን​ዘብ አይ​ቈ​ጣ​ጠ​ሩ​አ​ቸ​ውም ነበር።


ምሕ​ረ​ቱም ለዘ​ለ​ዓ​ለም ነውና እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ያመ​ሰ​ግኑ ዘንድ ኤማ​ን​ንና ኤዶ​ታ​ምን፥ በስ​ማ​ቸው የተ​ጻ​ፉ​ትን ተመ​ር​ጠው የቀ​ሩ​ትን ከእ​ነ​ርሱ ጋር አቆመ።


አራቱ ሺህም በረ​ኞች ነበሩ፤ አራቱ ሺህም ለም​ስ​ጋና በተ​ሠ​ሩት በዜማ ዕቃ​ዎች እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ያመ​ሰ​ግኑ ነበር።


መባ​ኡ​ንና ዐሥ​ራ​ቱን፥ የተ​ቀ​ደ​ሱ​ት​ንም በእ​ም​ነት ወደ​ዚያ አገቡ። ሌዋ​ዊ​ውም ኮክ​ን​ያስ ተሾ​መ​ባ​ቸው፥ ወን​ድ​ሙም ሰሜኢ በማ​ዕ​ርግ ሁለ​ተኛ ነበረ፤


ኢያ​ሱም፥ ልጆ​ቹም ተሾሙ፤ ወን​ድ​ሞ​ቹም፥ የይ​ሁ​ዳም ልጆች ቀደ​ም​ያ​ልና ልጆቹ፥ የኢ​ን​ሐ​ዳ​ድም ልጆች፥ ልጆ​ቻ​ቸ​ውና ወን​ድ​ሞ​ቻ​ቸው ሌዋ​ው​ያ​ንም የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቤት የሚ​ሠ​ሩ​ትን ያሠሩ ዘንድ በአ​ን​ድ​ነት ቆሙ።


ወን​ድ​ሜን ሃና​ኒ​ንና የግ​ን​ቡን አለቃ ሐና​ን​ያ​ንም በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ላይ ሾም​ኋ​ቸው፤ እር​ሱም እው​ነ​ተኛ ከሌ​ሎ​ቹም ይልቅ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የሚ​ፈራ ሰው ነበረ።


ለቀ​ዓ​ትም የእ​ን​በ​ረም ወገን፥ የይ​ስ​ዓር ወገን፥ የኬ​ብ​ሮ​ንም ወገን፥ የአ​ዛ​ሔ​ልም ወገን ነበሩ፤ የቀ​ዓት ወገ​ኖች እነ​ዚህ ናቸው።


እን​ግ​ዲህ በዚህ ከመ​ጋ​ቢ​ዎች እያ​ን​ዳ​ንዱ ቸርና ታማኝ ሆኖ እን​ዲ​ገኝ ይፈ​ለ​ጋል።