ነፍሴ በተማረረች ጊዜ፣ ልቤም በተቀሠፈ ጊዜ፣
ልቤ ነድዶአልና፥ ኩላሊቴም ቀልጦአልና፥
ኅሊናዬን በጣም መረረው፤ ልቤም ተሰበረ።
ችግረኛ አፍሮ አይመለስ፤ ድሃና ምስኪን ስምህን ያመሰግናሉ።
የርሱ ቀስተኞች ከበቡኝ፤ ያለ ርኅራኄ ኵላሊቴን ይበጣጥሳል፤ ሐሞቴን መሬት ላይ ያፈስሳል።
ዐመፀኞችን በማየት አትሸበር፤ በክፉ አድራጊዎችም አትቅና፤
በእግዚአብሔር ፊት ጸጥ በል፤ በትዕግሥትም ተጠባበቀው፤ መንገዱ በተቃናለት፣ ክፋትንም በሚሸርብ ሰው ልብህ አይሸበር።
ክፉዎች ሲሳካላቸው አይቼ፣ በዐመፀኞች ቀንቼ ነበርና።
ፍላጻዎችን ከሰገባው አውጥቶ፣ ልቤን ወጋው።