በዋስትና ቃል እጅ አትምታ፤ ለብድር ተያዥ አትሁን፤
የምር ቃል እንደሚገቡ፥ ለባለ ዕዳዎች እንደሚዋሱ አትሁን፥
የሌላ ሰው ዕዳ ለመክፈል ዋስ አትሁን፤
የሰውን ፊት በማፈር ራስህን ለዋስትና አትስጥ።
ለማይታወቅ ሰው ዋስ የሚሆን መከራ ያገኘዋል፤ ዋስትና ለመስጠት እጅ የማይመታ ግን ምንም አይደርስበትም።
ልበ ቢስ ሰው ሰው ቃል በመግባት እጅ ይመታል፤ ለወዳጁም ዋስ ይሆናል።
ለማይታወቅ ሰው ዋስ የሆነውን ልብሱን ግፈፈው፤ ለባዕድ ሴት የተዋሰውን በቃሉ ዐግተው።