Biblia Todo Logo
የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች

- ማስታወቂያዎች -



21 የቅዱሳን መጽሐፍ ጥቅሶች፡- በራዕይ መጽሐፍ ውስጥ

21 የቅዱሳን መጽሐፍ ጥቅሶች፡- በራዕይ መጽሐፍ ውስጥ

ቅድስና ማለት ለአንድ አላማና ዕቅድ ብቻ የተለየና የተቀደሰ መንፈሳዊ ልብስ ነው። ከእግዚአብሔር ጋር በተያያዘ፣ ለእርሱ ራስን መጠበቅ እና በኃጢአት ከሚመጣ ርኩሰት ሁሉ መራቅ የሚጠይቅ ግብ ነው።

ይህ ክፍል እስከ ዘመን ፍጻሜ ድረስ ለእግዚአብሔር ታማኝ ሆነው የሚኖሩትን እና የዘላለም ሕይወት የሚያገኙትን ቅዱሳንን ያመለክታል። ለብዙ አማኞች፣ የራእይ መጽሐፍ ቅዱሳን በዓለም ፈተናዎችና መከራዎች መካከል የቤዛነትና የተስፋ ቃል ምልክት ናቸው።

የእግዚአብሔር ቃል በራእይ መጽሐፍ (ራእይ 5:8) እንደሚለው፣ የቅዱሳኑን ጸሎት በዕጣን በተሞሉ የወርቅ ጽዋዎች ይይዛል። አባታችን ሆይ፣ ጸሎታችንን ፈጽሞ ስለማትረሳ እናመሰግንሃለን።




ራእይ 14:12

የእግዚአብሔርን ትእዛዞች የሚጠብቁና ለኢየሱስም ታማኝ ሆነው በትዕግሥት የሚጸኑ ቅዱሳን የሚታወቁት በዚህ ነው።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ራእይ 4:8

አራቱም ሕያዋን ፍጡራን እያንዳንዳቸው ስድስት ስድስት ክንፎች ነበሯቸው፤ በዙሪያቸውና በውስጣቸው በዐይኖች የተሞሉ ነበሩ፤ ቀንና ሌሊትም፦ “ቅዱስ፣ ቅዱስ፣ ቅዱስ፣ የነበረው፣ ያለውና የሚመጣው፤ ሁሉን ቻይ ጌታ አምላክ” ማለትን አያቋርጡም።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ራእይ 6:10

እነርሱም በታላቅ ድምፅ፣ “ሁሉን የምትገዛ ቅዱስና እውነተኛ ጌታ ሆይ፤ እስከ መቼ አትፈርድም? እስከ መቼስ ደማችንን በምድር በሚኖሩት ላይ አትበቀልም?” አሉ።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ራእይ 13:7

ቅዱሳንን እንዲዋጋና ድልም እንዲነሣቸው ኀይል ተሰጠው። በነገድ፣ በወገን፣ በቋንቋና በሕዝብም ሁሉ ላይ ሥልጣን ተሰጠው።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ራእይ 16:6

የቅዱሳንንና የነቢያትን ደም ስላፈሰሱ፣ አንተም ደግሞ ደም እንዲጠጡ አደረግሃቸው፤ ይህ የሚገባቸው ነውና።”

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ራእይ 20:6

በመጀመሪያው ትንሣኤ ተካፋይ የሚሆኑ ብፁዓንና ቅዱሳን ናቸው። ሁለተኛው ሞት በእነርሱ ላይ ሥልጣን የለውም፤ ነገር ግን የእግዚአብሔርና የክርስቶስ ካህናት ይሆናሉ፤ ከርሱም ጋራ ሺሕ ዓመት ይነግሣሉ።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ራእይ 8:3

ሌላም መልአክ የወርቅ ጥና ይዞ መጣና በመሠዊያው አጠገብ ቆመ፤ እርሱም በዙፋኑ ፊት ባለው የወርቅ መሠዊያ ላይ ከቅዱሳን ጸሎት ሁሉ ጋራ እንዲያቀርበው ብዙ ዕጣን ተሰጠው።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ራእይ 5:8

መጽሐፉን በወሰደ ጊዜ አራቱ ሕያዋን ፍጡራን፣ ሃያ አራቱ ሽማግሌዎችም በበጉ ፊት በግንባራቸው ተደፉ፤ እያንዳንዳቸውም የቅዱሳን ጸሎት የሆኑትን በገናና ዕጣን የሞላበትን የወርቅ ሙዳይ ይዘው ነበር።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ራእይ 22:11

ዐመፀኛው በዐመፁ ይቀጥል፤ ርኩሱም ይርከስ፤ ጻድቁም ይጽደቅ፤ ቅዱሱም ይቀደስ።”

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ራእይ 6:9

ዐምስተኛውን ማኅተም በፈታ ጊዜ፣ ስለ እግዚአብሔር ቃልና ስለ ጠበቁትም ምስክርነት የታረዱትን ሰዎች ነፍሶች ከመሠዊያው በታች አየሁ።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ራእይ 15:4

ጌታ ሆይ፤ አንተን የማይፈራ፣ ስምህን የማያከብርስ ማን ነው? አንተ ብቻ ቅዱስ ነህና። የጽድቅ ሥራህ ስለ ተገለጠ፣ ሕዝቦች ሁሉ ይመጣሉ፤ በፊትህም ይሰግዳሉ።”

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ራእይ 7:13-14

ከዚያም ከሽማግሌዎቹ አንዱ፣ “እነዚህ ነጭ ልብስ የለበሱት እነማን ናቸው? ከወዴትስ መጡ?” አለኝ።እኔም፣ “ጌታ ሆይ፤ አንተ ታውቃለህ” አልሁት። እርሱም እንዲህ አለኝ፤ “እነዚህ ከታላቁ መከራ የመጡ ናቸው፤ ልብሳቸውንም በበጉ ደም ዐጥበው አንጽተዋል።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ራእይ 11:18

አሕዛብ ተቈጥተው ነበር፤ የአንተም ቍጣ መጣች፤ በሙታን ላይ የምትፈርድበት፣ ለባሮችህ ለነቢያት፣ ለቅዱሳንና ስምህን ለሚፈሩት፣ ለታናናሾችና ለታላላቆች ዋጋቸውን የምትሰጥበት፣ ምድርንም ያጠፏትን የምታጠፋበት ዘመን መጣ።”

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ራእይ 12:11

እነርሱም በበጉ ደም፣ በምስክርነታቸውም ቃል፣ ድል ነሡት፤ እስከ ሞት ድረስ እንኳ፣ ለነፍሳቸው አልሳሱም።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ራእይ 17:6

ሴቲቱንም በቅዱሳን ደምና በኢየሱስ ምስክሮች ደም ሰክራ አየኋት። ባየኋትም ጊዜ እጅግ ተደነቅሁ።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ራእይ 18:20

“ሰማይ ሆይ፤ በርሷ ላይ ሐሤት አድርግ! ቅዱሳን፣ ሐዋርያትና ነቢያትም ሐሤት አድርጉ! በእናንተ ላይ ባደረሰችው ነገር እግዚአብሔር ፈርዶባታልና።”

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ራእይ 19:8

የሚያንጸባርቅና ንጹሕ፣ ከተልባ እግር የተሠራ ቀጭን ልብስ እንድትለብስ ተሰጣት።” ከተልባ እግር የተሠራው ቀጭን ልብስ የቅዱሳን የጽድቅ ሥራ ነው።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ራእይ 20:4

ቀጥሎም ዙፋኖችን አየሁ፤ በዙፋኖቹም ላይ ለመፍረድ ሥልጣን የተሰጣቸው ሰዎች ተቀምጠው ነበር፤ ደግሞም ስለ ኢየሱስ ምስክርና ስለ እግዚአብሔር ቃል የተሰየፉትን ሰዎች ነፍሶች አየሁ። እነርሱ ለአውሬው ወይም ለርሱ ምስል አልሰገዱም፤ በግንባራቸው ወይም በእጃቸው ላይ የአውሬውን ምልክት አልተቀበሉም፤ እነርሱም ከሞት ተነሥተው ከክርስቶስ ጋራ ሺሕ ዓመት ነገሡ።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ራእይ 21:24

ሕዝቦች በብርሃኗ ይመላለሳሉ፤ የምድር ነገሥታትም ክብራቸውን ወደ እርሷ ያመጣሉ።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ራእይ 22:6

መልአኩም፣ “እነዚህ ቃሎች የታመኑና እውነተኞች ናቸው። የነቢያት መናፍስት ጌታ አምላክ በቅርብ የሚሆነውን ነገር ለባሮቹ እንዲያሳይ መልአኩን ልኳል” አለኝ።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ

ወደ እግዚአብሔር ጸሎት

እግዚአብሔር ሆይ አመሰግንሃለሁ። ስለማይለወጥ ፍቅርህና ታላቅ ታማኝነትህ አመሰግንሃለሁ። ሕይወቴን ይቅር ብለህ ከጨለማ ወደ አስደናቂ ብርሃንህ አውጥተኸኛል። በኢየሱስ ክርስቶስ ስም፥ በደምህ ስለጸደቅሁ አመሰግንሃለሁ። የዚህን ዓለም ከንቱ ሥርዓት እንዳልከተል፥ በጽድቅ እንድኖርና ቅድስናን እንድፈጽም እርዳኝ። እንደ ቃልህ በቅድስና ለመኖር በጸሎት ጸንቼ እንድተጋ እርዳኝ። መንፈስ ቅዱስ ሆይ፥ ቃልህን በሕይወቴ ጠብቄ እንድኖር፥ ደፋርና የማልታክት እንድሆን እርዳኝ። እስከ መጨረሻው ድረስ ድል አድርጌ፥ ከአንተ ጋር የመገናኘትን ታላቅ ቀን እንዳይ፥ ከቅዱሳንህ ጋርም ሆኜ በትዕግሥት የምንጠብቀውን ተስፋ እንድቀበል እርዳኝ። በወርቅ ጎዳናዎች ላይ ከአንተ ጋር ለመራመድና ለመንገሥ በጉጉት እጠባበቃለሁ። በኢየሱስ ክርስቶስ ስም። አሜን!
ተከተሉን:

ማስታወቂያዎች


ማስታወቂያዎች