Biblia Todo Logo
የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች
- ማስታወቂያዎች -


100 የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች፡ ሲኦል ወይም ገሃነም

100 የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች፡ ሲኦል ወይም ገሃነም

የሞት ቦታ ወይም ሁኔታ ስለ ክፉዎች የመጨረሻ ቅጣት ሳይሆን፣ ቃሉ ከአረማውያን አፈታሪክ የተወሰደ ቢሆንም፣ ትርጉሙ የመጣው ከዕብራይስጥ ቃል ሲኦል ነው። ሲኦል በብሉይ ኪዳን ስልሳ አምስት ጊዜ ተጠቅሷል፣ እና በአንዳንድ ትርጉሞች ሲኦል፣ መቃብር ወይም ጉድጓድ ተብሎ ቢተረጎምም፣ በአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ ግን ሲኦል እንደነበረው ተጽፎ እናገኘዋለን። ልክ እንደ ሲኦል፣ ሐዲስ የሚለውም ቃል ከግሪክ የተወሰደ ነው።

ኢየሱስ ለጴጥሮስ “የሲኦል ደጆች በቤተክርስቲያን ላይ አይበረቱም” እንዳለው ማስታወስ አስፈላጊ ነው። ይህ ማለት ኢየሱስ ለቤተክርስቲያን በጠላት ኃይል ላይ ሥልጣን ሰጥቶ፣ እርሱ ሕይወት ባዘዘበት ቦታ ላይ ሞትን እንዳንናገር ኃይል ሰጥቶናል። ስለዚህ፣ የእግዚአብሔርን ፈቃድ በምድር ላይ ለማጽናት ቤተክርስቲያን ሁልጊዜ በጸሎት እና በቃሉ መቆም ያስፈልጋታል።


ሐዋርያት ሥራ 2:27

ነፍሴን በሲኦል አትተዋትምና፤ ቅዱስህም መበስበስን እንዲያይ አትፈቅድም።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ማቴዎስ 16:18

አንተ ጴጥሮስ ነህ፤ በዚህ ዐለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ፤ የገሃነም ደጆችም አያሸንፏትም።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ሐዋርያት ሥራ 2:31

ይህን አስቀድሞ በማየቱ እርሱ በሲኦል እንዳልቀረና ሥጋውም መበስበስን እንዳላየ ስለ ክርስቶስ ትንሣኤ ተናገረ።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ሉቃስ 10:15

አንቺም ቅፍርናሆም፤ ወደ ሰማይ ከፍ ከፍ ልትዪ ነውን? ወደ ሲኦል ትወርጃለሽ።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ሉቃስ 16:23

በሲኦልም እየተሠቃየ ሳለ ቀና ብሎ ከሩቅ አብርሃምን አየ፤ አልዓዛርንም በዕቅፉ ይዞት አየ።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ራእይ 1:18

እኔ ሕያው ነኝ፤ ሞቼ ነበር፤ እነሆ፤ አሁን ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ ሕያው ነኝ፤ የሞትና የሲኦል መክፈቻም በእጄ ነው።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ራእይ 20:13

ባሕርም በውስጡ የነበሩትን ሙታን ሰጠ፤ ሞትና ሲኦልም በእነርሱ ውስጥ የነበሩትን ሙታን ሰጡ፤ እያንዳንዱም እንደ ሥራው መጠን ተፈረደበት።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ማቴዎስ 5:22

እኔ ግን እላችኋለሁ፤ ወንድሙን ያለ አግባብ የሚቈጣ ይፈረድበታል፤ ማንም ወንድሙን ‘ጅል’ የሚል በሸንጎ ፊት ይጠየቅበታል፤ ‘ደደብ’ የሚለው ደግሞ የገሃነመ እሳት ፍርድ ይጠብቀዋል።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ማቴዎስ 11:23

አንቺም ቅፍርናሆም፤ ወደ ሰማይ ከፍ ከፍ ልትዪ ነውን? ወደ ሲኦል ትወርጃለሽ፤ በአንቺ የተደረገው ታምራት በሰዶም ቢደረግ ኖሮ፣ እስከ ዛሬ በቈየች ነበር።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ራእይ 6:8

እኔም ተመለከትሁ፤ እነሆ፤ ግራጫ ፈረስ ቆሞ አየሁ፤ ተቀምጦበት የነበረውም ስሙ ሞት ነበር፤ ሲኦልም ከኋላ ይከተለው ነበር። እነርሱም በሰይፍ፣ በራብ፣ በመቅሠፍትና በምድር አራዊት እንዲገድሉ በምድር አንድ አራተኛ ላይ ሥልጣን ተሰጣቸው።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ማቴዎስ 10:28

ሥጋን መግደል እንጂ ነፍስን መግደል የማይችሉትን አትፍሩ፤ ይልቁንስ ነፍስንና ሥጋን በገሃነም ማጥፋት የሚቻለውን ፍሩ።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ራእይ 20:13-14

ባሕርም በውስጡ የነበሩትን ሙታን ሰጠ፤ ሞትና ሲኦልም በእነርሱ ውስጥ የነበሩትን ሙታን ሰጡ፤ እያንዳንዱም እንደ ሥራው መጠን ተፈረደበት። ከዚያም በኋላ ሞትና ሲኦል ወደ እሳት ባሕር ተጣሉ፤ የእሳቱ ባሕር ሁለተኛው ሞት ነው።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ማቴዎስ 23:33

“እናንተ እባቦች፤ የእፉኝት ልጆች! ከገሃነም ፍርድ እንዴት ልታመልጡ ትችላላችሁ?

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ሉቃስ 16:24

እርሱም፣ ‘አብርሃም አባት ሆይ፤ ራራልኝ፤ በዚህ ነበልባል እየተሠቃየሁ ስለ ሆነ፣ አልዓዛር የጣቱን ጫፍ ውሃ ነክሮ ምላሴን እንዲያቀዘቅዝልኝ እባክህ ላክልኝ’ እያለ ጮኸ።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ሉቃስ 16:26

ከሁሉም በላይ ከዚህ ወደ እናንተ ለማለፍ የሚፈልጉ እንደማይችሉ፣ እዚያ ያሉትም ደግሞ ወደ እኛ እንዳይሻገሩ፣ በእኛና በእናንተ መካከል ትልቅ ገደል ተደርጓል።’

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ሉቃስ 16:28

ዐምስት ወንድሞች ስላሉኝ፣ እነርሱም ወደዚህ የሥቃይ ስፍራ እንዳይመጡ ያስጠንቅቃቸው።’

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ሮሜ 6:23

የኀጢአት ደመወዝ ሞት ነውና፤ የእግዚአብሔር ስጦታ ግን በጌታችን በክርስቶስ ኢየሱስ የዘላለም ሕይወት ነው።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
2 ቆሮንቶስ 5:10

ሁላችንም በክርስቶስ የፍርድ ወንበር ፊት እንቀርባለንና፤ እያንዳንዱም ሰው በሥጋው ለሠራው በጎ ወይም ክፉ ሥራ ተገቢውን ዋጋ ይቀበላል።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ገላትያ 6:7

አትታለሉ፤ እግዚአብሔር አይዘበትበትም። ሰው የሚዘራውን ያንኑ ያጭዳል።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ፊልጵስዩስ 3:19

መጨረሻቸው ጥፋት ነው፤ ሆዳቸው አምላካቸው ነው፤ ክብራቸው በነውራቸው ነው፤ ሐሳባቸው በምድራዊ ነገር ላይ ነው።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ዕብራውያን 9:27

ሰው አንድ ጊዜ ሊሞት ከዚያም በኋላ በፍርድ ፊት ሊቆም ተወስኖበታል።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ዕብራውያን 10:27

የሚቀረው ግን የሚያስፈራ ፍርድና የእግዚአብሔርን ጠላቶች የሚበላ ብርቱ እሳት መጠበቅ ብቻ ነው።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ያዕቆብ 3:6

ምላስም እንደ እሳት ናት፤ በሰውነት ክፍሎቻችን መካከል የምትገኝ የክፋት ዓለም ናት፤ ሰውነትን ሁሉ ታረክሳለች፤ ደግሞም የፍጥረትን ሩጫ ታቃጥላለች፤ ራሷም በገሃነም ትቃጠላለች።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
1 ጴጥሮስ 3:19

በመንፈስም ሄዶ በወህኒ ቤት ለነበሩ ነፍሳት ሰበከላቸው።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
1 ጴጥሮስ 4:6

ወንጌል ለሙታን እንኳ ሳይቀር የተሰበከው በዚህ ምክንያት ነው፤ ስለዚህ እንደ ማንኛውም ሰው በሥጋ ይፈረድባቸዋል፤ በመንፈስ ግን እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ይኖራሉ።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ራእይ 2:11

መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚናገረውን ጆሮ ያለው ይስማ፤ ድል የሚነሣም በሁለተኛው ሞት ከቶ አይጐዳም።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ራእይ 20:10

ያሳታቸው ዲያብሎስም፣ አውሬውና ሐሰተኛው ነቢይ ወዳሉበት ወደ እሳቱና ወደ ዲኑ ባሕር ተጣለ፤ እነርሱም ቀንና ሌሊት ከዘላለም እስከ ዘላለም ይሠቃያሉ።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ራእይ 20:14

ከዚያም በኋላ ሞትና ሲኦል ወደ እሳት ባሕር ተጣሉ፤ የእሳቱ ባሕር ሁለተኛው ሞት ነው።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ራእይ 21:8

ነገር ግን ፈሪዎች፣ የማያምኑ፣ ርኩሶች፣ ነፍሰ ገዳዮች፣ አመንዝሮች፣ አስማተኞች፣ ጣዖት አምላኪዎች፣ ውሸተኞች ሁሉ ዕጣ ፈንታቸው በዲንና በእሳት ባሕር ውስጥ መጣል ይሆናል። ይህም ሁለተኛው ሞት ነው።”

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ኢሳይያስ 14:9

በመጣህ ጊዜ ሲኦል ልትቀበልህ ተነሣሥታለች፤ ይቀበሉህም ዘንድ የሙታንን መናፍስት፣ በዓለም ገዥ የነበሩትን ሁሉ ቀስቅሳለች፤ በአሕዛብ ላይ የነገሡትን ነገሥታት ከዙፋናቸው አውርዳለች።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ኢሳይያስ 14:15

ነገር ግን ወደ ሲኦል፣ ወደ ጥልቁም ጕድጓድ ወርደሃል።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ኢሳይያስ 66:24

“ወጥተውም በእኔ ላይ ያመፁትን ሰዎች ሬሳ ያያሉ፤ የሚበሏቸው ትሎች አይሞቱም፤ የሚያቃጥላቸው እሳታቸው አይጠፋም፤ ለሰውም ዘር ሁሉ አስጸያፊ ይሆናሉ።”

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ሕዝቅኤል 32:21

በመቃብርም ውስጥ ኀያላኑ መሪዎች ስለ ግብጽና ስለ ተባባሪዎቿ፣ ‘ወደ ታች ወርደዋል፤ በሰይፍ ከተገደሉትና ካልተገረዙትም ጋራ በአንድ ላይ ተጋድመዋል’ ይላሉ።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ሕዝቅኤል 32:27

ከዘመናት በፊት ከወደቁት ከኀያላን ሰዎች፣ ከእነዚያ ሰይፋቸውን ተንተርሰው፣ ጋሻቸውንም ደረታቸው ላይ ይዘው ከነሙሉ ትጥቃቸው ወደ መቃብር ከወረዱት ጋራ አይጋደሙምን? የእነዚህ ተዋጊዎች ሽብር በሕያዋን ምድር ባሉት ያልተገረዙ ኀያላን ላይ ቢደርስም፣ የኀጢአታቸው ቅጣት በዐጥንታቸው ላይ ይሆናል።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ዳንኤል 12:2

በምድር ዐፈር ውስጥ ካንቀላፉት ብዙዎች ይነቃሉ፤ አንዳንዶቹ ለዘላለም ሕይወት፣ ሌሎቹም ለውርደትና ለዘላለም ጕስቍልና ይነሣሉ።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ማቴዎስ 8:12

መንግሥተ ሰማይ ተዘጋጅቶላቸው የነበሩት ግን ወደ ውጭ ወደ ጨለማው ይጣላሉ። በዚያም ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል።”

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ማቴዎስ 22:13

“ንጉሡም አገልጋዮቹን፣ ‘እጅና እግሩን አስራችሁ በውጭ ወዳለው ጨለማ አውጥታችሁ ጣሉት፤ በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል’ አላቸው፤

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ማቴዎስ 24:51

ይቈራርጠዋል፤ ዕድል ፈንታውንም ከግብዞች ጋራ ያደርግበታል፤ በዚያም ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ማቴዎስ 25:30

ይህን የማይረባ ባሪያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ወዳለበት በውጭ ወዳለው ጨለማ አውጥታችሁ ጣሉት’ አለ።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ሉቃስ 12:5

ነገር ግን መፍራት የሚገባችሁን አሳያችኋለሁ፤ ከገደለ በኋላ ወደ ገሃነም ለመጣል ሥልጣን ያለውን እርሱን ፍሩት፤ አዎን፣ እርሱን ፍሩት እላችኋለሁ።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ሉቃስ 13:28

“አብርሃምን፣ ይሥሐቅንና ያዕቆብን፣ ነቢያትንም ሁሉ በእግዚአብሔር መንግሥት ውስጥ ስታዩ፣ እናንተ ግን ወደ ውጭ ተጥላችሁ ስትቀሩ፣ በዚያ ጊዜ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ሉቃስ 16:19

ደግሞም ኢየሱስ እንዲህ አለ፤ “ሐምራዊና ቀጭን በፍታ የለበሰ፣ በየቀኑም በተድላ ደስታ የሚኖር አንድ ሀብታም ሰው ነበረ።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ሮሜ 1:18

በክፋታቸው እውነትን ዐፍነው በሚይዙ፣ በዐመፃቸውና በክፋታቸው ሁሉ ላይ የእግዚአብሔር ቍጣ ከሰማይ ይገለጣል፤

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ሮሜ 2:8

ነገር ግን በራስ ወዳዶች፣ እውነትን ትተው ክፋትን በሚከተሉ ፍርድና ቍጣ ይደርስባቸዋል።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ሮሜ 2:9

ክፉ በሚያደርግ በማንኛውም ሰው፣ አስቀድሞ በአይሁድ ከዚያም በአሕዛብ ላይ መከራና ጭንቀት ይሆናል፤

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
2 ተሰሎንቄ 1:9

እነርሱም ከጌታ ፊትና ከኀይሉ ክብር ተወግደው በዘላለም ጥፋት ይቀጣሉ፤

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ራእይ 14:11

የሥቃያቸውም ጢስ ከዘላለም እስከ ዘላለም ወደ ላይ ይወጣል። ለአውሬውና ለምስሉ የሚሰግዱ ወይም የስሙንም ምልክት የሚቀበሉ ሁሉ ቀንና ሌሊት ዕረፍት የላቸውም።”

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ራእይ 20:15

ስሙ በሕይወት መጽሐፍ ተጽፎ ያልተገኘ ሁሉ ወደ እሳት ባሕር ተጣለ።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
መዝሙር 9:17

ክፉዎች ተመልሰው ወደ ሲኦል ይወርዳሉ፤ እግዚአብሔርን የሚዘነጉ ሕዝቦችም ሁሉ እንደዚሁ።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
መዝሙር 55:15

ሞት ሳይታሰብ ድንገት ይምጣባቸው፤ በሕይወት ሳሉ ወደ ሲኦል ይውረዱ፤ ክፋት በመካከላቸው ዐድራለችና።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
መዝሙር 86:13

ለእኔ ያሳየሃት ምሕረት ታላቅ ናትና፤ ነፍሴንም ከሲኦል ጥልቀት አውጥተሃል።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ምሳሌ 15:24

ወደ ሲኦል ከመውረድ እንዲድን፣ የሕይወት መንገድ ጠቢቡን ሰው ወደ ላይ ትመራዋለች።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ምሳሌ 27:20

ሲኦልና የሙታን ዓለም እንደማይጠግቡ ሁሉ፣ የሰውም ዐይን አይረካም።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ኢሳይያስ 5:14

ስለዚህ ሲኦል ሆዷን አሰፋች፣ አፏንም ያለ ልክ ከፈተች፤ መኳንንቱና ሕዝቡ ከረብሸኞቻቸውና ከጨፋሪዎቻቸው ጋራ ወደዚያ ይወርዳሉ።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ኢሳይያስ 28:15

እናንተ፣ “ከሞት ጋራ ቃል ኪዳን ገብተናል፤ ከሲኦልም ጋራ ስምምነት አድርገናል፤ ውሸትን መጠጊያችን፣ ሐሰትን መደበቂያችን አድርገናል፤ ታላቅ መቅሠፍት እየጠራረገ ሲያልፍ፣ ሊነካን አይችልም” በማለት ታብያችኋል።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ኢሳይያስ 30:33

ከቀድሞ ጀምሮ ቶፌት የተባለ የማቃጠያ ስፍራ ተዘጋጅቷል፤ ለንጉሡም ተበጅቷል፤ ማንደጃ ጕድጓዱም ሰፊና ጥልቅ ነው፤ በውስጡም ብዙ እሳትና ማገዶ አለ፤ የእግዚአብሔርም እስትንፋስ እንደ ፈሳሽ ድኝ ያቀጣጥለዋል።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ሰቈቃወ 3:55

በጥልቁ ጕድጓድ ውስጥ ሳለሁ፣ እግዚአብሔር ሆይ፤ የአንተን ስም ጠራሁ።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ሕዝቅኤል 18:30

“የእስራኤል ቤት ሆይ፤ ስለዚህ እንደየሥራችሁ በእያንዳንዳችሁ ላይ እፈርዳለሁ፤ ይላል ጌታ እግዚአብሔር። እንግዲህ ንስሓ ግቡ፤ በኀጢአት እንዳትጠፉ፣ ከኀጢአታችሁ ሁሉ ተመለሱ።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ሕዝቅኤል 33:11

እንዲህ በላቸው፤ ‘በሕያውነቴ እምላለሁ፤ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፤ ከመንገዳቸው ተመልሰው በሕይወት እንዲኖሩ እንጂ በክፉዎች ሞት ደስ አልሰኝም። ተመለሱ! ከክፉ መንገዳችሁ ተመለሱ! የእስራኤል ቤት ሆይ፤ ለምን ትሞታላችሁ?’

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ሆሴዕ 13:14

“ከመቃብር ኀይል እታደጋቸዋለሁ፤ ከሞትም እቤዣቸዋለሁ፤ ሞት ሆይ፤ መቅሠፍትህ የት አለ? መቃብር ሆይ፤ ማጥፋትህ የት አለ? “ከእንግዲህ ወዲህ አልራራለትም፤

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ሚክያስ 1:5

ይህ ሁሉ የሚሆነው ስለ ያዕቆብ በደል፣ ስለ እስራኤልም ቤት ኀጢአት ነው። የያዕቆብ በደል ምንድን ነው? ሰማርያ አይደለችምን? የይሁዳስ የኰረብታ መስገጃ ምንድን ነው? ኢየሩሳሌም አይደለችምን?

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ዕንባቆም 3:14

እንደ ዐውሎ ነፋስ ሊበታትነን የመጣውን፣ ምስኪኑን በስውር በመዋጥ የሚደሰተውን፣ የሰራዊት አለቃ ራስ፣ በገዛ ጦሩ ወጋህ።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ማቴዎስ 7:13

“በጠባቡ በር ግቡ፤ ወደ ጥፋት የሚወስደው መንገድ ትልቅ፣ በሩም ሰፊ ነውና፤ ብዙዎችም በዚያ ይገባሉ።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ማቴዎስ 13:42

ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ወዳለበት ወደ እቶን እሳት ይጥሏቸዋል።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ማቴዎስ 13:50

ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ወዳለበት ወደ እቶን እሳት ይጥሏቸዋል።”

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ማቴዎስ 25:41

“ከዚያም በግራው በኩል ላሉት ደግሞ እንዲህ ይላቸዋል፤ ‘እናንተ የተረገማችሁ፤ ለዲያብሎስና ለመላእክቱ ወደ ተዘጋጀው የዘላለም እሳት ከእኔ ተለይታችሁ ሂዱ፤

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ሉቃስ 9:25

ሰው ዓለምን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱን ግን ቢያጠፋ ወይም ቢያጐድል ጥቅሙ ምንድን ነው?

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ዮሐንስ 3:36

በወልድ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት አለው፤ በወልድ የማያምን ግን የእግዚአብሔር ቍጣ በላዩ ይሆናል እንጂ ሕይወትን አያይም።”

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ዮሐንስ 8:24

በኀጢአታችሁ እንደምትሞቱ ነግሬአችኋለሁ፤ እኔ እርሱ ነኝ ስላችሁ እኔ እርሱ እንደ ሆንሁ ካላመናችሁ፣ በኀጢአታችሁ ትሞታላችሁና።”

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ሮሜ 8:1

ስለዚህ በክርስቶስ ኢየሱስ ያሉት አሁን ኵነኔ የለባቸውም፤

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
1 ቆሮንቶስ 6:9

ዐመፀኞች የእግዚአብሔርን መንግሥት እንደማይወርሱ አታውቁምን? በዚህ ነገር አትታለሉ፤ ሴሰኞች፣ ጣዖት አምላኪዎች፣ አመንዝሮች፣ ወንደቃዎች፣ ግብረ ሰዶማውያን፣

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
1 ቆሮንቶስ 15:22

ሰዎች ሁሉ በአዳም እንደሚሞቱ፣ እንደዚሁም ሰዎች ሁሉ በክርስቶስ ሕያዋን ይሆናሉ፤

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ገላትያ 5:19-21

የሥጋ ሥራ ግልጽ ነው፦ ይኸውም ዝሙት፣ ርኩሰት፣ መዳራት፣ የምለውን አስተውሉ! ትገረዙ ዘንድ ብትፈልጉ፣ ክርስቶስ ፈጽሞ ለእናንተ እንደማይበጃችሁ እኔ ጳውሎስ እነግራችኋለሁ። ጣዖትን ማምለክ፣ ሟርት፣ ጥላቻ፣ ጠብ፣ ቅናት፣ ቍጣ፣ ራስ ወዳድነት፣ መለያየት፣ ዐድመኛነት፣ ምቀኛነት፣ ስካር፣ ዘፋኝነት፣ እንዲሁም እነዚህን የመሰለው ነው። አስቀድሜ እንዳልሁ፣ አሁንም አስጠነቅቃችኋለሁ፤ በእንዲህ ሁኔታ የሚኖሩ ሁሉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ኤፌሶን 5:5

ደግሞም ይህን ዕወቁ፤ ማንም አመንዝራ ወይም ርኩስ ወይም ስግብግብ፣ ይኸውም ጣዖት አምላኪ በክርስቶስና በእግዚአብሔር መንግሥት ርስት የለውም።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ቈላስይስ 3:6

በእነዚህም ምክንያት የእግዚአብሔር ቍጣ በማይታዘዙት ላይ ይመጣል፤

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ዕብራውያን 6:4-6

አንድ ጊዜ ብርሃን የበራላቸውን፣ ሰማያዊውን ስጦታ የቀመሱትን፣ ከመንፈስ ቅዱስ ተካፋዮች የሆኑትን፣ መልካሙን የእግዚአብሔር ቃልና የሚመጣውን ዓለም ኀይል የቀመሱትን፣ በኋላ ግን የካዱትን እንደ ገና ወደ ንስሓ መመለስ አይቻልም፤ ምክንያቱም እነርሱ ለገዛ ጥፋታቸው የእግዚአብሔርን ልጅ እንደ ገና ይሰቅሉታል፤ ያዋርዱታልም።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ዕብራውያን 12:29

“አምላካችን የሚባላ እሳት ነውና።”

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ያዕቆብ 4:12

ሕግን የሚሰጥና የሚፈርድ አንድ ብቻ ነው፤ እርሱም ሊያድንና ሊያጠፋ የሚችል ነው፤ ነገር ግን በባልንጀራህ ላይ የምትፈርድ አንተ ማን ነህ?

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
1 ዮሐንስ 2:15-17

ዓለምን ወይም በዓለም ያለውን ማንኛውንም ነገር አትውደዱ፤ ማንም ዓለምን ቢወድድ የአብ ፍቅር በርሱ ዘንድ የለም፤ ምክንያቱም በዓለም ያለው ሁሉ፦ የሥጋ ምኞት፣ የዐይን አምሮትና የኑሮ ትምክሕት ከዓለም እንጂ ከአብ የሚመጣ አይደለም። ዓለምና ምኞቱ ያልፋሉ፤ የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚፈጽም ግን ለዘላለም ይኖራል።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ራእይ 3:5

ድል የሚነሣም እንደ እነርሱ ነጭ ልብስ ይለብሳል፤ እኔም በአባቴና በመላእክቱ ፊት እመሰክርለታለሁ፤ ስሙንም ከሕይወት መጽሐፍ አልደመስስም።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ራእይ 3:16

እንግዲህ ለብ ያልህ ብቻ እንጂ ትኵስ ወይም ቀዝቃዛ ስላልሆንህ ከአፌ አውጥቼ ልተፋህ ነው።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
መዝሙር 37:20

ክፉዎች ግን ይጠፋሉ፤ የእግዚአብሔር ጠላቶች እንደ መስክ ውበት ይሆናሉ፤ ይጠፋሉ፤ እንደ ጢስም ተነው ይጠፋሉ።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
መዝሙር 49:14

እንደ በጎች ለሲኦል የተዳረጉ ናቸው፤ ሞትም እረኛቸው ይሆናል፤ ቅኖች በማለዳ ይገዟቸዋል፤ አካላቸው ከክብር ቤታቸው ርቆ፣ በሲኦል ይፈራርሳል።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
መዝሙር 73:27

እነሆ፤ ከአንተ የሚርቁ ይጠፋሉና፤ አንተ የሚያመነዝሩትን ሁሉ ታጠፋቸዋለህ።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ምሳሌ 9:18

እነርሱ ግን ሙታን በዚያ እንዳሉ፣ ተጋባዦቿም በሲኦል ጥልቀት ውስጥ እንደ ሆኑ አያውቁም።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ምሳሌ 10:7

የጻድቃን መታሰቢያቸው በረከት ነው፤ የክፉዎች ስም ግን እንደ ጠፋ ይቀራል።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
መክብብ 9:10

እጅህ የሚያገኘውን ሥራ ሁሉ በሙሉ ኀይልህ ሥራው፤ ልትሄድበት ባለው መቃብር ውስጥ መሥራትም ሆነ ማቀድ፣ ዕውቀትም ሆነ ጥበብ የለምና።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ኢሳይያስ 57:21

አምላኬ፣ “ለክፉዎች ሰላም የላቸውም” ይላል።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ኤርምያስ 7:34

የደስታና የተድላን ድምፅ፣ የሙሽራና የሙሽራዪቱን ድምፅ ከይሁዳ ከተሞችና ከኢየሩሳሌም መንገዶች አጠፋለሁ፤ ምድሪቱ ባድማ ትሆናለችና።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ሰቈቃወ 2:22

“በበዓል ቀን ለግብዣ እንደምትጠራ፣ ሽብርን ከየአቅጣጫው በእኔ ላይ ጠራህ፤ በእግዚአብሔር የቍጣ ቀን፣ ማንም አላመለጠም ወይም አልተረፈም፤ የተንከባከብኋቸውንና ያሳደግኋቸውን፣ ጠላቴ አጠፋብኝ።”

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ሕዝቅኤል 31:17

ከአሕዛብ መካከል ከርሱ ጋራ ያበሩ፣ በጥላው ሥር የኖሩ፣ በሰይፍ ከሞቱት ጋራ ለመቀላቀል ወደ መቃብር ወርደዋል።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ሕዝቅኤል 32:11

“ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና፤ “ ‘የባቢሎን ንጉሥ ሰይፍ፣ በአንተ ላይ ይመጣል።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ማቴዎስ 12:36

ነገር ግን እላችኋለሁ፤ ሰዎች ስለ ተናገሩት ከንቱ ቃል ሁሉ በፍርድ ቀን ይጠየቁበታል።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ማቴዎስ 13:30

ተዉአቸው፤ እስከ መከር ጊዜ ዐብረው ይደጉ። በዚያ ጊዜ ዐጫጆቹን እንክርዳዱን አስቀድማችሁ ንቀሉ፤ በእሳትም እንዲቃጠል በየነዶው እሰሩት፤ ስንዴውን ግን ሰብስባችሁ በጐተራዬ ክተቱ እላቸዋለሁ’ አላቸው።”

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ሉቃስ 8:31

አጋንንቱም እንጦርጦስ ግቡ ብሎ እንዳያዝዛቸው አጥብቀው ለመኑት።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ሮሜ 1:32

ይህን የሚያደርጉ ሁሉ ሞት ይገባቸዋል የሚለውን ትክክለኛ የሆነውን የእግዚአብሔርን ሕግ ቢያውቁም፣ እነዚህን ነገሮች ማድረግ ብቻ ሳይሆን፣ እንዲህ የሚያደርጉትንም ያበረታታሉ።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
2 ተሰሎንቄ 2:12

ይህም የሚሆነው እውነትን ያላመኑት ነገር ግን በክፋት ደስ ይላቸው የነበሩ ሁሉ እንዲፈረድባቸው ነው።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ዕብራውያን 10:31

በሕያው እግዚአብሔር እጅ መውደቅ እጅግ የሚያስፈራ ነው።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ
ራእይ 19:20

ነገር ግን አውሬው ተያዘ፤ ከርሱም ጋራ በፊቱ ምልክቶችን ያደርግ የነበረው ሐሰተኛው ነቢይ ተያዘ። በእነዚህ ምልክቶች የአውሬውን ምልክት የተቀበሉትንና ለምስሉ የሰገዱትን አሳተ። ሁለቱም በሕይወት እንዳሉ በዲን ወደሚቃጠለው የእሳት ባሕር ተጣሉ።

ምዕራፍ    |  ስሪቶች ቅዳ

ወደ እግዚአብሔር ጸሎት

እግዚአብሔር ሆይ፥ ስምህ ቅዱስና የሚያስፈራ ነው፤ ከቅድስናህ ጋር የሚተካከል የለም። ዛሬ ተጸጽቼ ይቅርታ እጠይቃለሁ፤ ከክፋትና ከፍርሃት ነፃ ሊያወጣኝ የሚችለው መገኘትህ ብቻ እንደሆነ አውቃለሁ። ሕይወቴ በፊትህ መልካም መዓዛ እንዲሆንና እርምጃዎቼም በድምጽህ እንዲመሩ ትጉህና ኃላፊነት የሚሰማው ልጅህ አድርገኝ። ጌታ ኢየሱስ ሆይ፥ ዛሬ ኃጢአቴን አምኜ በፊትህ እሰግዳለሁ፤ እባክህ ጌታ ሆይ፥ መንገዱ ያደረሰብኝን ቁስል ፈውሰኝ፤ አድሰኝ፤ ነፍሴ በሲኦል ለዘላለም እንዳትሰቃይ። ትናንት እንደመጣህና ነገ እንደምትመለስ በማሰብ በየቀኑ እንድጠብቅህ እርዳኝ። ጌታ ሆይ፥ ርኩሰት፥ እድፍና ከንቱነት ዓይኔን ከአንተ እንዲያርቁ አትፍቀድ። ቃልህ «ነፍሴን በሲኦል አትተዋትም፥ ቅዱስህም መበስበስን አያይም» ይላል። በኢየሱስ ስም። አሜን!
ተከተሉን:

ማስታወቂያዎች


ማስታወቂያዎች