Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ ጦቢት 6 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


መል​አ​ኩና ጦብያ ወደ ጤግ​ሮስ ወንዝ እንደ ደረ​ሱና ዓሣ እንደ ያዙ

1 በመ​ን​ገ​ዳ​ቸ​ውም ሲሄዱ ወደ ጤግ​ሮስ ወንዝ ማታ ደረሱ፤ በዚ​ያም አደሩ።

2 ያም ልጅ ሊታ​ጠብ ወረደ፤ ከው​ኃ​ውም ውስጥ ዓሣ ወጥቶ ተወ​ረ​ወረ፤ ያንም ልጅ ይው​ጠው ዘንድ ወደደ።

3 መል​አ​ኩም፥ “ያን ዓሣ ያዘው” አለው፤ ያም ልጅ ዓሣ​ውን ያዘው፤ ወደ የብ​ስም አወ​ጣው።

4 ያም መል​አክ፥ “ዓሣ​ውን እረ​ደው፤ ልቡ​ንና ጉበ​ቱን፥ ሐሞ​ቱ​ንም ያዝ፤ አጥ​ብ​ቀ​ህም ጠብቅ” አለው።

5 ያም ልጅ መል​አኩ እን​ዳ​ዘ​ዘው አደ​ረገ፤ ዓሣ​ው​ንም ጠብ​ሰው በሉ፤ ሁለ​ቱም ገሥ​ግ​ሠው ሄደው፥ ወደ በጣ​ኔስ ደረሱ።

6 ያም ልጅ መል​አ​ኩን አለው፥ “አንተ ወን​ድሜ አዛ​ርያ! የዚህ ዓሣ ልቡ፥ ጉበ​ቱና ሐሞቱ ለም​ን​ድን ነው?”

7 መል​አ​ኩም አለው፥ “ልቡና ጉበቱ፦ የሚ​ያ​ሳ​ምም ክፉ ጋኔን ያደ​ረ​በት ቢኖር፥ ወይም ርኩስ መን​ፈስ ያደ​ረ​በት ቢኖር ያን ለዚያ ሰው በፊቱ ያጤ​ሱ​ለ​ታል፤ ሴትም ብት​ሆን ያጤ​ሱ​ላ​ታል፤ ከዚ​ያም በኋላ አይ​ታ​መ​ሙም።

8 ሐሞ​ቱን ግን በዐ​ይኑ ላይ ብልዝ ያለ​በ​ትን ሰው ይኩ​ሉ​ታል፤ እር​ሱም ይድ​ናል።”

9 ወደ ራጊ​ስም በቀ​ረቡ ጊዜ፥

10 መል​አኩ አለው፥ “አንተ ወን​ድሜ! ዛሬ በራ​ጉ​ኤል ቤት እና​ድ​ራ​ለን፤ እር​ሱም ዘመ​ድህ ነው፤ አን​ዲት ልጅም አለ​ችው፤ ስሟም ሳራ ይባ​ላል፤ ሚስት ትሆ​ንህ ዘንድ እን​ዲ​ሰ​ጥህ ስለ እር​ስዋ እና​ገ​ራ​ለሁ፤ ለአ​ንተ ውርሷ ይደ​ር​ስ​ሃ​ልና።

11 ከዘ​መ​ዶ​ች​ዋም ወገን አንተ አለህ፤ ልጂ​ቱም ደግና ልባም ናት።

12 አሁ​ንም ስማኝ፤ ለአ​ባ​ት​ዋም እነ​ግ​ረ​ዋ​ለሁ፤ ከራ​ጊ​ስም በተ​መ​ለ​ስን ጊዜ የሠ​ርግ በዓል እና​ደ​ር​ጋ​ለን፤ ራጉ​ኤል፦ በሙሴ ሕግ መሠ​ረት ለሌላ ሰው ይሰ​ጣት ዘንድ አይ​ወ​ድ​ድ​ምና፥ ብት​ሞ​ትም በወ​ደደ ነበር፤ከሰው ሁሉ ይልቅ ውርሷ ላንተ ይደ​ር​ስ​ሃ​ልና።”

13 ያም ልጅ መል​አ​ኩን አለው፥ “አንተ ወን​ድሜ አዛ​ርያ! ያቺን ልጅ ለሰ​ባት ወን​ዶች እን​ዳ​ጋ​ቧት እኔ ሰም​ቻ​ለሁ፤ ሁሉም በሠ​ርጉ ጊዜ ሞቱ።

14 አሁ​ንም እኔ ላባቴ ብቸኛ ነኝ፤ ወደ እር​ሷም በገ​ባሁ ጊዜ እን​ዳ​ል​ሞት ፥ ያባ​ቴ​ንና የና​ቴ​ንም ሕይ​ወት በእኔ ምክ​ን​ያት በጭ​ንቅ ወደ መቃ​ብር እን​ዳ​ላ​ወ​ርድ እፈ​ራ​ለሁ፤ የሚ​ቀ​ብ​ራ​ቸ​ውም ሌላ ልጅ የላ​ቸ​ው​ምና።”

15 ያም መል​አክ አለው፥ “ከዘ​መ​ዶ​ችህ ሚስት ታገባ ዘንድ አባ​ትህ ያዘ​ዘ​ህን ቃል አታ​ስ​ብ​ምን? አሁ​ንም አንተ ወን​ድሜ ስማኝ፤ የጋ​ኔኑ ነገ​ርስ አያ​ሳ​ዝ​ንህ፤ በዚች ሌሊት ከዘ​መ​ዶ​ችህ ወገን እርሷ ሚስት ሆና ትሰ​ጥ​ሃ​ለ​ችና፤

16 ወደ ጫጕላ ቤትም በገ​ባህ ጊዜ የዕ​ጣን ዕራሪ ውሰድ፤ ከዚ​ህም ዓሣ ከጉ​በ​ቱና ከልቡ ጨም​ረህ አጢ​ስ​በት።

17 ጋኔ​ኑም በሸ​ተ​ተው ጊዜ ይሸ​ሻል፤ ለዘ​ለ​ዓ​ለ​ሙም አይ​መ​ለ​ስም። ወደ እር​ሷም በገ​ባህ ጊዜ ሁለ​ታ​ችሁ ይቅር ባይ ወደ ሆነው ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጩኹ፤ እር​ሱም ያድ​ና​ች​ኋል፤ ይቅ​ርም ይላ​ች​ኋል። እን​ግ​ዲህ አት​ፍራ፤ ከጥ​ንት ጀምሮ እር​ሷን አዘ​ጋ​ጅ​ቶ​ል​ሃ​ልና፤ አን​ተም ታድ​ና​ታ​ለህ፤ እር​ሷም ካንተ ጋራ ትሄ​ዳ​ለች፤ ከእ​ር​ሷም ልጆ​ችን እን​ደ​ም​ት​ወ​ልድ እነ​ግ​ር​ሃ​ለሁ፤” ጦብ​ያም ይህን ሰምቶ አደ​ነቀ፤ ልቡም ወደ እርሷ ተሳበ፤ ወደ ባጥ​ናም ደረሱ።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች