Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ ጦቢት 3 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


የጦ​ቢት ጸሎት

1 ከዚ​ህም በኋላ በልብ ጭን​ቀት ተከ​ዝሁ፤ አል​ቅ​ሼም ጸለ​ይሁ።

2 እን​ዲ​ህም አልሁ፥ “አቤቱ በሥ​ራህ ሁሉ በቸ​ር​ነ​ትና በፍ​ርድ፥ በሚ​ገባ ጽድ​ቅም አንተ እው​ነ​ተኛ ነህ፤ አቤቱ አንተ በሚ​ገባ ዓለ​ምን ትገ​ዛ​ለህ።

3 አስ​በኝ፤ ተመ​ል​ከ​ተ​ኝም፤ በራሴ ኀጢ​አ​ትና አን​ተን በበ​ደሉ፥ ትእ​ዛ​ዝ​ህ​ንም ባል​ሰሙ በአ​ባ​ቶች ኀጢ​አት አት​በ​ቀ​ለኝ።

4 ለመ​በ​ር​በ​ርና ለመ​ማ​ረክ፥ ለመ​ገ​ደ​ልም አደ​ረ​ግ​ኸን፤ በዓ​ለሙ ሁሉና በው​ስ​ጣ​ቸው በተ​በ​ተ​ን​ባ​ቸው በአ​ሕ​ዛ​ብም ዘንድ መተ​ረ​ቻና መዘ​ባ​በቻ ሆንን።

5 አሁ​ንም እው​ነ​ተኛ ፍር​ድህ ብዙ ነው፤ የእኔ ኀጢ​አ​ትና የአ​ባ​ቶች ኀጢ​አ​ትም እን​ዲ​ሰ​ረይ አድ​ር​ግ​ልኝ፤ ትእ​ዛ​ዝ​ህን አላ​ደ​ረ​ግ​ን​ምና፥ በፊ​ት​ህም በእ​ው​ነት አል​ሄ​ድ​ን​ምና።

6 አሁ​ንም በፊ​ትህ ደስ የሚ​ያ​ሰ​ኝ​ህን በእኔ አድ​ርግ፤ ከመ​ኖር መሞት ይሻ​ለ​ኛ​ልና በሞት እሰ​ና​በት ዘንድ፥ መሬ​ትም እሆን ዘንድ ነፍ​ሴን የሚ​ቀ​በ​ላ​ትን እዘ​ዝ​ልኝ። በሐ​ሰ​ትና በው​ር​ደት ተግ​ዳ​ሮ​ትን ሰም​ቻ​ለ​ሁና፥ ኀዘ​ንም በእኔ ላይ በዝ​ት​ዋ​ልና ከመ​ከ​ራዬ እሰ​ና​በት ዘንድ፥ ወደ ዘለ​ዓ​ለ​ማዊ ቦታም እሄድ ዘንድ እዘዝ፤ ፊት​ህ​ንም ከእኔ አት​መ​ልስ።”

7 በዚ​ያ​ችም ቀን በሜ​ዶን ክፍል በጣ​ኔስ የራ​ጉ​ኤል ልጅ ሣራን ከአ​ባ​ትዋ ሴቶች አገ​ል​ጋ​ዮች ተግ​ዳ​ሮት አገ​ኛት።

8 ለሰ​ባት ወን​ዶች አጋ​ብ​ተ​ዋት እንደ ወን​ድና ሴት ሳይ​ቃ​ረቡ አስ​ማ​ን​ድ​ዮስ የሚ​ባል ክፉ ጋኔን ገድ​ሏ​ቸ​ዋ​ልና፤ እን​ዲ​ህም አሏት፥ “ባሎ​ችሽ እየ​ታ​ነቁ እን​ደ​ሚ​ሞቱ አታ​ው​ቂ​ምን፦ እነሆ ሰባቱ አገ​ቡሽ፤ ከእ​ነ​ር​ሱም አንዱ ስንኳ አል​ተ​ከ​ተ​ለ​ሽም።

9 እን​ግ​ዲህ ስለ እነ​ርሱ ምን አሳ​ዘ​ነን? እነ​ርሱ ሞተ​ዋ​ልና ከእ​ነ​ርሱ ጋር ሂጂ፤ ከአ​ንቺ ወንድ ወይም ሴት ልጅ እስከ ዘለ​ዓ​ለሙ ድረስ አንይ።”

10 ይህ​ንም በሰ​ማች ጊዜ ለመ​ታ​ነቅ እስ​ከ​ም​ት​መኝ ድረስ እጅግ አዘ​ነች። እን​ዲ​ህም አለች፥ “እኔ ለአ​ባ​ቴና ለእ​ናቴ አን​ዲት ነኝ፤ እን​ደ​ዚ​ህም ባደ​ርግ ተግ​ዳ​ሮት እሆ​ን​በ​ታ​ለሁ፤ ሽም​ግ​ል​ና​ው​ንም፥ ሰው​ነ​ቱ​ንም በጭ​ንቅ ወደ መቃ​ብር አወ​ር​ዳ​ታ​ለሁ።”


የሣራ ጸሎት

11 በመ​ስ​ኮ​ቱም በኩል ጸለ​የች፤ እን​ዲ​ህም አለች፥ “አቤቱ አንተ ፈጣ​ሪዬ ቡሩክ ነህ፤ ቅዱ​ስና ክቡር ስም​ህም ለዘ​ለ​ዓ​ለም ይመ​ስ​ገን፤ ሥራ​ህም ሁሉ ለዘ​ለ​ዓ​ለሙ ክቡር ነው።

12 አቤቱ አሁ​ንም ዐይ​ኖ​ች​ንና ፊቴን ለአ​ንተ ሰጠሁ።

13 እን​ግ​ዲህ ወዲህ ተግ​ዳ​ሮ​ትን እን​ዳ​ል​ሰማ ከዚህ ዓለም አሰ​ና​ብ​ተኝ አል​ኹህ።

14 ከወ​ንድ ጋር ከሚ​ሠ​ራው ኀጢ​አት ሁሉ እኔ ንጽ​ሕት እንደ ሆንኹ አቤቱ አንተ ታው​ቃ​ለህ።

15 በተ​ማ​ረ​ክ​ሁ​በ​ትም ሀገር ስሜ​ንና ያባ​ቴን ስም አላ​ሳ​ደ​ፍ​ሁም፤ እኔም ለአ​ባቴ አን​ዲት ነኝ። ወን​ድም የለ​ኝም፤ ሚስት እሆ​ን​ለት ዘንድ የም​ጠ​ብ​ቀው የቅ​ርብ ዘመ​ድም የለ​ኝም፤ ሰባቱ ባሎች ሙተ​ው​ብ​ኛ​ልና እን​ግ​ዲህ ለምን እኖ​ራ​ለሁ? ልት​ገ​ድ​ለኝ ባት​ወድ ግን ወደ እኔ ተመ​ል​ክ​ተህ ራራ​ልኝ፤ ተግ​ዳ​ሮ​ት​ንም እን​ዳ​ል​ሰማ እዘ​ዝ​ልኝ።”

16 የሁ​ለ​ቱም ጸሎ​ታ​ቸው በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በገ​ነነ ጌት​ነቱ ፊት ተሰማ።

17 ሩፋ​ኤ​ል​ንም ላከው፤ ሁለ​ቱን ያድ​ና​ቸው ዘንድ፥ ከጦ​ቢ​ትም ዐይን ብል​ዙን ያጠ​ፋ​ለት ዘንድ፥ የራ​ጉ​ኤል ልጅ ሳራ​ንም ሚስት ልት​ሆ​ነው ለጦ​ቢት ልጅ ለጦ​ብያ ይሰ​ጣት ዘንድ፥ ክፉ ጋኔን አስ​ማ​ን​ድ​ዮ​ስ​ንም ይሽ​ረው ዘንድ፥ ጦብያ ይወ​ር​ሳ​ታ​ልና። በዚ​ያም ወራት ጦቢት ተመ​ልሶ ወደ ቤቱ ገባ፤ የራ​ጉ​ኤል ልጅ ሳራም ከሰ​ገ​ነቷ ወረ​ደች።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች