Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ ጦቢት 2 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 ወደ ሀገ​ሬም በተ​መ​ለ​ስሁ ጊዜ ሚስ​ቴን ሐና​ንና ልጄን ጦብ​ያን መለ​ሰ​ልኝ። በሰ​ባ​ተ​ኛው ሱባኤ በተ​ቀ​ደ​ሰ​ችው የበ​ዓለ ኀምሳ ዕለት ለእኔ መል​ካም ነገር አደ​ረ​ጉ​ልኝ፤ እበ​ላም ዘንድ ተቀ​መ​ጥሁ።

2 ምግ​ቡም እጅግ ብዙ እንደ ሆነ ባየሁ ጊዜ ልጄን እን​ዲህ አል​ሁት፥ “ሄደህ ከወ​ን​ድ​ሞ​ቻ​ችን ያገ​ኘ​ሃ​ቸ​ውን ድኆች ባል​ን​ጀ​ሮ​ችን አምጣ። እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን አስ​ቤ​ዋ​ለ​ሁና። እነሆ እኔም እጠ​ብ​ቅ​ሃ​ለሁ።”

3 በተ​መ​ለሰ ጊዜም እን​ዲህ አለኝ፥ “አባቴ! ከወ​ገ​ኖ​ቻ​ችን የተ​ገ​ደለ አንድ ሰው አገ​ኘሁ፤ ሬሳ​ውም በገ​በያ ወድ​ቆ​አል።”

4 እኔም እህል ሳል​ቀ​ምስ ተነ​ሣሁ፤ ፀሐ​ይም እስ​ኪ​ገባ ድረስ ወደ አንዱ ቤት አገ​ባ​ሁት።

5 ወደ ቤቴም ተመ​ልሼ ታጥቤ ምግ​ቤን በኀ​ዘን በላሁ።

6 አሞ​ፅም፥ “በዓ​ላ​ችሁ ወደ ኀዘን፥ ደስ​ታ​ች​ሁም ወደ ልቅሶ ይመ​ለ​ሳል” ያለ​ውን አስ​ታ​ወ​ስሁ።

7 ከዚ​ህም በኋላ አለ​ቀ​ስሁ፤ ፀሐ​ይም በገባ ጊዜ ሄጄ መቃ​ብር ቆፍሬ ቀበ​ር​ሁት።

8 ጎረ​ቤ​ቶ​ችም ሳቁ​ብኝ፤ እን​ዲ​ህም አሉ፥ “ይህ ሰው ስለ​ዚህ ሥራ እገ​ደ​ላ​ለሁ ብሎ አይ​ፈ​ራ​ምን? ንጉሥ የገ​ደ​ላ​ቸ​ውን ይቀ​ብ​ራ​ልና።”


የጦ​ቢት ዐይን እን​ዴት እንደ ታወረ

9 በዚ​ያ​ችም ሌሊት ከቀ​ብር ተመ​ለ​ስሁ፤ ረክ​ሼም ስለ​ነ​በር በዕ​ድ​ሞው ሥር አደ​ርሁ፤ ዓይ​ኖች ግን ተገ​ል​ጠው ነበር።

10 በዕ​ድ​ሞው ላይም ወፎች እን​ዳሉ አላ​ወ​ቅ​ሁም፤ ፊቴም ተገ​ልጦ ሳለ እነ​ዚያ ወፎች በዐ​ይኔ ላይ የሚ​ያ​ቃ​ጥል ኩስ ጣሉ​ብኝ፤ በዐ​ይ​ኔም ብልዝ ወጣ​ብኝ፤ እኔም ወደ ባለ መድ​ኀ​ኒት ሄድሁ፥ ነገር ግን የጠ​ቀ​መኝ የለም፤ ብቻ​ዬን ወደ ኤል​ማ​ድያ እስ​ክ​ሄድ ድረስ አኪ​አ​ክ​ሮስ ይመ​ግ​በኝ ነበር።

11 ሐናም በሴ​ቶች ቤት ታገ​ለ​ግል ነበር።

12 ወደ እመ​ቤ​ቶ​ች​ዋም ላከች፤ እነ​ር​ሱም ደመ​ወ​ዟን ሰጧት፤ የበግ ጠቦ​ትም ጨመ​ሩ​ላት።

13 ወደ እኔም በመ​ጣች ጊዜ ትጮህ ጀመር፤ እኔም እን​ዲህ አል​ኋት፥ “ይቺ ጠቦት ከወ​ዴት ናት? የሰ​ረ​ቅ​ሻት ከሆ​ነ​ችም ወደ ጌቶ​ችዋ መል​ሻት። የተ​ሰ​ረቀ መብ​ላት አግ​ባብ አይ​ደ​ለ​ምና።”

14 እር​ሷም አለ​ችኝ፥ “በደ​መ​ወዜ ላይ ሰጡኝ፤” እኔ ግን አላ​መ​ን​ኋ​ትም፤ ለባ​ለ​ቤ​ቶ​ቹም መልሺ ብዬ ከእ​ርሷ ጋር ተከ​ራ​ከ​ርሁ፤ እር​ሷም መልሳ፥ “ጸሎ​ት​ህና ምጽ​ዋ​ትህ ወዴት ነው? እነሆ በላ​ይህ ያለው ሁሉ ታወቀ” አለ​ችኝ።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች