Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽሐፈ ሲራክ 9 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ስለ ሴቶች የተ​ሰጠ ምክር

1 ክፉ ትም​ህ​ር​ትን እን​ዳ​ት​ማ​ር​ብህ፥ ባጠ​ገ​ብህ የም​ተ​ተኛ ሚስ​ት​ህን አታ​ስ​ቀ​ናት።

2 ኀይ​ል​ህን እን​ዳ​ታ​ደ​ክ​ም​ብህ፥ ለሴት ልብ​ህን አት​ስ​ጣት።

3 በወ​ጥ​መ​ድዋ እን​ዳ​ት​ያዝ የሌላ ሚስት አታ​ባ​ብል።

4 በዘ​ፈኗ እን​ዳ​ታ​ስ​ትህ ከዘ​ፋኝ ሴት ጋር አት​ጫ​ወት።

5 ፈቃዷ እን​ዳ​ያ​ስ​ትህ ድን​ግ​ልን አት​ቈ​ን​ጥ​ጣት።

6 ርስ​ት​ህን እን​ዳ​ታጣ ለአ​መ​ን​ዝራ ልቡ​ና​ህን አት​ስ​ጣት።

7 በከ​ተ​ማ​ዎቹ መን​ገድ ዙሪያ አታ​ማ​ትር፤ አደ​ባ​ባ​ይ​ዋም አያ​ስ​ትህ።

8 ከመ​ልከ መል​ካም ሴት ዐይ​ን​ህን መልስ፤ የሌላ ሚስ​ትም ደም ግባ​ትዋ አያ​ስ​ጐ​ም​ጅህ፤ በሴት ደም ግባት የሳቱ ሰዎች ብዙ​ዎች ናቸ​ውና፤ ስለ​ዚህ ነገር ፍቅሯ እንደ እሳት ይነ​ድ​ዳል።

9 ከጐ​ል​ማሳ ሚስት ጋር አት​ቀ​መጥ፤ ልቡ​ና​ህን ወደ እርሷ እን​ዳ​ት​ወ​ስድ፥ ሰው​ነ​ት​ህ​ንም በሞት እን​ዳ​ታ​ሰ​ነ​ካ​ክል በመ​ጠጥ ጊዜ ከእ​ርሷ ጋር አት​ቀ​መጥ።

10 ድን​ገ​ተኛ ወዳጅ እንደ እርሱ አይ​ሆ​ን​ህ​ምና፥ የቀ​ድሞ ወዳ​ጅ​ህን አት​ተ​ወው። አዲስ ወዳጅ ጉሽ ጠጅ ነው፤ ቢከ​ርም ግን ደስ ብሎህ ትጠ​ጣ​ዋ​ለህ።

11 እን​ደ​ሚ​ጠፉ አታ​ው​ቅ​ምና የኃ​ጥ​ኣን ብል​ጽ​ግ​ና​ቸው አያ​ስ​ቀ​ናህ።

12 የክ​ፉ​ዎች ሰዎ​ችም ተድ​ላ​ቸው አያ​ስ​ጐ​ም​ጅህ፤ እስ​ኪ​ሞ​ቱም ድረስ እን​ደ​ማ​ይ​ከ​ብሩ ዐስብ።

13 በሞት ከሚ​ቀጡ መኳ​ን​ንት ፈጽ​መህ ራቅ፤ ሰው​ነ​ት​ህን እን​ዳ​ታ​ጠፋ የሞት ጥር​ጥር አያ​ግ​ኝህ፥ ነገር ግን በወ​ጥ​መድ መካ​ከል እን​ደ​ም​ት​ሄድ፥ በገ​ደ​ልም መካ​ከል እን​ደ​ም​ት​መ​ላ​ለስ ዕወቅ።

14 የተ​ቻ​ለ​ህን ያህል ለባ​ል​ን​ጀ​ራህ መል​ካም አድ​ር​ግ​ለት፤ ከጠ​ቢ​ባ​ንም ጋር ተማ​ከር።

15 ጉዳ​ይ​ህም ከዐ​ዋ​ቂ​ዎች ጋር ይሁን፤ ነገ​ርህ ሁሉ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሕግ ይሁ​ን​ልህ።

16 ድሆች ሰዎች በም​ሳሕ ጊዜ ይኑሩ፤ ክብ​ር​ህም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን በመ​ፍ​ራት ይሁን።

17 ሥራው በብ​ል​ሃ​ተ​ኛው እጅ ይከ​ና​ወ​ናል፤ የአ​ሕ​ዛ​ብ​ንም አለቃ በቃሉ ጥበብ ያመ​ሰ​ግ​ኑ​ታል።

18 ተና​ጋሪ ሰው በከ​ተ​ማው አስ​ፈሪ ነው፥ ከቃ​ሉም የተ​ነሣ ፈጽሞ ይጠ​ላል።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች