Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽሐፈ ሲራክ 8 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 በእ​ጃ​ቸው እን​ዳ​ት​ወ​ድቅ ከታ​ላ​ላ​ቆች ሰዎች ጋር አት​ከ​ራ​ከር።

2 በብ​ል​ጽ​ግ​ናው ድል እን​ዳ​ያ​ደ​ር​ግህ ከባ​ለ​ጸጋ ጋር አት​ጣላ፥ ብዙ​ዎች ስለ ወርቅ ጠፍ​ተ​ዋ​ልና፤ የነ​ገ​ሥ​ታ​ትም ልቡና ድል ሆኖ​አ​ልና።

3 ከተ​ና​ጋሪ ሰውም ጋር አት​ከ​ራ​ከር፤ ያለ​ዚያ በእ​ሳት ላይ እን​ጨት መከ​መ​ርህ ነው።

4 እና​ትና አባ​ት​ህን እን​ዳ​ታ​ዋ​ርድ፥ ከአ​ላ​ዋቂ ሰው ጋር አት​ሣቅ።

5 ከኀ​ጢ​አቱ የተ​መ​ለ​ሰ​ውን ሰው አት​ን​ቀ​ፈው፤ እኛ ሁላ​ች​ንም ኀጢ​አ​ተ​ኞች እን​ደ​ሆን ዐስብ።

6 በር​ጅ​ናው ጊዜ ሰውን አታ​ቅ​ል​ለው፥ ከእኛ የማ​ያ​ረጅ የለ​ምና።

7 በሞተ ሰው ደስ አይ​በ​ልህ፤ ሁላ​ች​ንም እን​ደ​ም​ን​ሞት ዐስብ።

8 የብ​ል​ሆ​ችን ነገር አታ​ቃ​ልል፤ ጥበ​ብን በእ​ነ​ርሱ ዘንድ ታገ​ኛ​ለ​ህና፥ ምሳ​ሌ​ያ​ቸ​ውን ተማር። መም​ህ​ራ​ን​ንም አገ​ል​ግል።

9 የሽ​ማ​ግ​ሎ​ችን ምክ​ራ​ቸ​ውን ጠብቅ፤ እነ​ርሱ ከአ​ባ​ቶ​ቻ​ቸው ተም​ረ​ዋ​ልና አን​ተም ከእ​ነ​ርሱ ተማር፤ በኀ​ዘ​ን​ህም ጊዜ የም​ት​ና​ገ​ረ​ውን ታገ​ኛ​ለህ የም​ት​መ​ል​ሰ​ው​ንም ታው​ቃ​ለህ።

10 በእ​ሳ​ታ​ቸው እን​ዳ​ት​ቃ​ጠል፥ የኀ​ጢ​አ​ተ​ኞች ሰዎ​ችን እሳት አት​ጫር።

11 በአ​ን​ደ​በቱ ነገር እን​ዳ​ያ​ስ​ትህ፥ በተ​ሳ​ዳ​ቢና በጠ​ላት ዘንድ አት​ከ​ራ​ከር።

12 ከአ​ንተ ለሚ​በ​ለ​ጽ​ገው አታ​በ​ድ​ረው፤ ብታ​በ​ድ​ረው ግን ገን​ዘ​ብ​ህን እን​ዳ​ጣህ ዕወቅ።

13 ከአ​ንተ ለሚ​በ​ረ​ታ​ውም አቷ​ሰው፤ ብቷ​ሰው ግን አንተ ራስህ እን​ደ​ም​ት​ከ​ፍል ዐስብ።

14 ከዳኛ ጋር አት​ከ​ራ​ከር፥ እንደ ክብሩ መጠን ፍር​ድን ይለ​ው​ጡ​ለ​ታ​ልና፤

15 እን​ዳ​ይ​ደ​ፍ​ርህ ከደ​ፋር ሰው ጋራ መን​ገ​ድን አት​ሂድ፤ እርሱ ልቡ እንደ ወደደ ያደ​ር​ጋ​ልና አን​ተም በእ​ርሱ ስን​ፍና ትሞ​ታ​ለህ።

16 ከቍጡ ሰው ጋር አት​ከ​ራ​ከር፤ በእ​ርሱ ዘንድ ደም ማፍ​ሰስ እንደ ኢም​ንት ነውና፥ ረዳት ወደ​ሌ​ለ​በት ቦታም ይወ​ስ​ድ​ሃ​ልና ከእ​ርሱ ጋር ወደ ምድረ በዳ አት​ውጣ።

17 የሰ​ማ​ውን ነገር መጠ​በቅ አይ​ች​ል​ምና፥ ከአ​ላ​ዋቂ ሰው ጋራ አት​ማ​ከር።

18 እን​ዴት እን​ደ​ሚ​ደ​ር​ስ​ብህ አታ​ው​ቅ​ምና፥ ጉዳ​ይ​ህን በባ​ዕድ ፊት አት​ና​ገር።

19 ዋጋህ እን​ዳ​ይ​ጠ​ፋ​ብህ፥ ለሰው ሁሉ የል​ብ​ህን ምሥ​ጢር አት​ግ​ለጥ።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች