Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽሐፈ ሲራክ 7 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 ክፋ​ትን አት​ሥ​ራት፤ ክፉም አያ​ገ​ኝ​ህም።

2 ከበ​ደል ራቅ፥ እር​ሷም ራስዋ ካንተ ትር​ቃ​ለች።

3 ሰባት እጥፍ አድ​ር​ገህ እን​ዳ​ት​ሰ​በ​ስ​ባት፥ በኀ​ጢ​አት ትልም አት​ዝራ።

4 ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መን​ግ​ሥ​ትን አት​ለ​ምን፤ ከን​ጉ​ሥም የክ​ብር ዙፋን አት​ለ​ምን።

5 በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ጻድቅ ነኝ አት​በል፤ በን​ጉ​ሥም ዘንድ ብልህ ነኝ አት​በል።

6 ዳኛ መሆ​ንን አት​ው​ደድ፤ እነሆ፥ በደ​ለ​ኛ​ውን ለመ​በ​ቀል አት​ች​ልም ይሆ​ናል፤ እነሆ፥ ለባ​ለ​ጸ​ጋም ታደላ ይሆ​ናል፤ በእ​ው​ነት ሥራ​ህም ላይ ኀጢ​አት ትሠ​ራ​ለህ።

7 ያገ​ር​ህ​ንም ሰው አት​በ​ድል፤ ራስ​ህ​ንም በወ​ገ​ኖ​ችህ መካ​ከል አታ​ስት።

8 በአ​ን​ዲ​ቱም ቢሆን ከቅ​ጣት አታ​መ​ል​ጥ​ምና፥ ሁለት ኀጢ​አት አንድ አድ​ር​ገህ አት​ሥራ።

9 በመ​ባዬ ብዛት እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ኀጢ​አ​ቴን ያስ​ተ​ሰ​ር​ይ​ል​ኛል፤ ለል​ዑል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም መባእ ከአ​ገ​ባሁ ይቅር ይለ​ኛል አት​በል።

10 በም​ት​ጸ​ል​ይ​በት ጊዜ አት​ቸ​ኩል፥ ምጽ​ዋት መመ​ጽ​ወ​ት​ንም አታ​ቃ​ልል።

11 የሚ​ያ​ሳ​ዝን፥ ደስ የሚ​ያ​ሰ​ኝም አለና፥ ባዘነ ሰው አት​ሳቅ።

12 በባ​ል​ን​ጀ​ራህ ሐሰ​ትን ተግ​ባር አታ​ድ​ርግ፤ በወ​ዳ​ጅ​ህና በባ​ል​ን​ጀ​ራ​ህም ላይ እን​ዲህ አታ​ድ​ርግ።

13 በም​ንም ሁል​ጊዜ ሐሰ​ትን አት​ው​ደድ፥ ፍጻ​ሜዋ ይጎ​ዳ​ሃ​ልና።

14 በሽ​ማ​ግ​ሌ​ዎች መካ​ከል ብዙ ቃል አት​ና​ገር፤ በአ​ፍህ የተ​ና​ገ​ር​ኸ​ውን ስእ​ለ​ት​ህን አት​መ​ልስ፥ ቃል​ህ​ንም አት​ለ​ውጥ።

15 የእ​ጅ​ህ​ንም ሥራ አታ​ቃ​ልል፥ ፈጣ​ሪ​ህም የሚ​ያ​በ​ቅ​ል​ል​ህን ቡቃ​ያ​ህን ቸል አት​በል።

16 ብዙ ናቸው ብለህ ከኀ​ጢ​አ​ተ​ኞች ጋር አንድ አት​ሁን።

17 ጥፋት እን​ደ​ማ​ት​ዘ​ገይ ዐስብ፥ ሰው​ነ​ት​ህን ፈጽ​መህ አዋ​ር​ዳት፥ የኀ​ጢ​አ​ተ​ኞች ፍዳ​ቸው ትልና እሳት ነውና።

18 በእ​የ​ነ​ጋው ወዳጅ አት​ለ​ውጥ፤ ስለ ቀይ ወርቅ ወዳ​ጅ​ህን አትጣ።

19 መወ​ደዷ ከወ​ርቅ ይወ​ደ​ዳ​ልና ብል​ህና ደግ ሴትን አት​ጥላ።

20 በእ​ው​ነት በሚ​ገ​ዛ​ልህ ቤተ ሰብህ ላይ፥ ስለ አንተ ሰው​ነ​ቱን አሳ​ልፎ በሚ​ሰጥ በም​ን​ደ​ኛ​ህም ላይ ክፉ ነገ​ርን አታ​ድ​ርግ።

21 ብልህ ቤተ ሰብ​ህን እንደ ራስህ ውደ​ደው፤ ነጻ ታወ​ጣ​ውም ዘንድ ተስፋ ያደ​ረ​ገ​ህን ዋጋ​ውን አታ​ጥ​ፋ​በት።

22 ሁል​ጊዜ ከብ​ት​ህን መፍ​ቀድ አት​ተው፤ ከእ​ነ​ርሱ የሚ​ጠ​ቅ​ም​ህን ወደ አንተ አቅ​ርብ።

23 ልጆች ቢኖ​ሩህ ምከ​ራ​ቸው፤ ከሕ​ፃ​ን​ነ​ታ​ቸው ጀም​ረህ ትሕ​ት​ናን አስ​ተ​ም​ራ​ቸው።

24 ሴቶች ልጆ​ችም ቢኖ​ሩህ ጠብ​ቃ​ቸው፤ አታ​ስ​ታ​ቸው፥ አት​ሣ​ቅ​ላ​ቸው፥ አታ​ባ​ብ​ላ​ቸ​ውም።

25 ልጅ​ህን አቅመ ሔዋን ስታ​ደ​ርስ አጋ​ባት፥ ጠብ​ቃት፥ ታላቅ ሥራ​ንም ትፈ​ጽ​ማ​ለህ፥ ከድ​ካ​ምም ታር​ፋ​ለህ፥ ነገር ግን ለብ​ልህ ሰው አጋ​ባት።

26 እንደ ራስህ የም​ት​ወ​ዳት ሚስት ብት​ኖ​ርህ አት​ፍ​ታት።

27 በፍ​ጹም ልቡ​ናህ አባ​ት​ህን አክ​ብ​ረው፥ የእ​ና​ት​ህ​ንም ምጧን አት​ዘ​ንጋ።

28 በእ​ነ​ር​ሱም ምክ​ን​ያት እንደ ተወ​ለ​ድህ ዐስብ፤ ስላ​ደ​ረ​ጉ​ል​ህስ ፋንታ ምን ታደ​ር​ግ​ላ​ቸ​ዋ​ለህ?

29 በፍ​ጹም ሰው​ነ​ትህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ፍራው፤ ካህ​ና​ቱ​ንም አክ​ብ​ራ​ቸው።

30 በፍ​ጹም ኀይ​ል​ህም ፈጣ​ሪ​ህን ውደ​ደው፤ የሚ​ያ​ገ​ለ​ግ​ሉ​ት​ንም አት​ተ​ዋ​ቸው።

31 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ፍራው፤ የሚ​ያ​ገ​ለ​ግ​ለ​ውን ካህ​ኑ​ንም አክ​ብ​ረው፤ የታ​ዘ​ዘ​ልህ ዕድ​ሉ​ንም ስጠው፤ ቀዳ​ም​ያ​ቱ​ንና፥ ስለ ኀጢ​አት የሚ​ሠ​ዋ​ውን መሥ​ዋ​ዕት፥ ወር​ቹ​ንም፥ ማታና ጧትም የሚ​ሠ​ዋ​ውን መሥ​ዋ​ዕት፥ መጀ​መ​ሪያ የሚ​ወ​ለ​ደ​ው​ንም ከብት ስጠው።

32 በረ​ከ​ትህ ፍጽ​ምት ትሆን ዘንድ እጅ​ህን ለድሃ ዘርጋ።

33 ስጦታ በሕ​ያው ሁሉ ፊት ጸጋ አለው፥ ስለ ሞተ ሰውም ምጽ​ዋት መስ​ጠ​ትን አት​ተው።

34 ከሚ​ያ​ለ​ቅሱ ሰዎ​ችም አት​ለይ፥ ከሚ​ያ​ለ​ቅ​ሱም ጋር አል​ቅስ።

35 ሕመ​ም​ተ​ኛ​ንም ሰው መጐ​ብ​ኘት ቸል አት​በል፥ በዚ​ህም ይወ​ዱ​ሃል።

36 በተ​ና​ገ​ር​ኸው ነገር ሁሉ ፍጻ​ሜ​ህን ዐስ​ባት፥ ሁል​ጊ​ዜም አት​በ​ድል።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች