Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽሐፈ ሲራክ 47 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ናታ​ንና ዳዊት

1 ከእ​ር​ሱም በኋላ ናታን ተነሣ፤ በዳ​ዊ​ትም ዘመን ትን​ቢት ተና​ገረ።

2 ስቡን ከድ​ኅ​ነቱ መሥ​ዋ​ዕት እን​ደ​ሚ​ለዩ እን​ደ​ዚሁ ዳዊት ከእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ተለየ።

3 በእ​ር​ሱም ዘንድ አን​በሳ እንደ ፍየል ጠቦት፥ ግስ​ላም እንደ በግ ጠቦት ነበር።

4 በወ​ጣ​ት​ነቱ አር​በ​ኛን የገ​ደለ አይ​ደ​ለ​ምን? እጁ​ንስ አን​ሥቶ ድን​ጋይ በወ​ነ​ጨፈ ጊዜ ጎል​ያ​ድን ግን​ባ​ሩን የመ​ታው፥ ናላ​ው​ንም የበ​ጠ​በ​ጠው አይ​ደ​ለ​ምን? የሕ​ዝ​ቡ​ንስ ተግ​ዳ​ሮት ያስ​ወ​ገደ አይ​ደ​ለ​ምን?

5 ልዑል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ለም​ኖ​ታ​ልና በሰ​ልፍ ኀይ​ለ​ኛ​ውን ሰው ይገ​ድል ዘንድ የወ​ገ​ኖ​ቹ​ንም ቀንድ ያጸና ዘንድ በቀኝ እጁ ኀይ​ልን ሰጠው።

6 ዘፋ​ኞ​ቹም ዳዊ​ትን ዐሥር ሺህ ገዳይ አሉት፤ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በረ​ከት አመ​ሰ​ገ​ኑት፤ የክ​ብር ዘው​ድ​ንም ተቀ​ዳጀ።

7 በዙ​ሪ​ያው ያሉ ጠላ​ቶ​ቹ​ንም ቀጠ​ቀ​ጣ​ቸው፤ ጠላ​ቶቹ ፍል​ስ​ጥ​ኤ​ማ​ው​ያ​ን​ንም አዋ​ረ​ዳ​ቸው፤ እስከ ዛሬም ድረስ ቀን​ዳ​ቸ​ውን ሰበረ።

8 በሚ​ሠ​ራው ሥራ ሁሉ ቅዱ​ስና ልዑል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን በም​ስ​ጋና ቃል አመ​ሰ​ገነ፤ በፍ​ጹም ልቡም ፈጣ​ሪ​ውን አመ​ሰ​ገ​ነው፤ ወደ​ደ​ውም።

9 በመ​ሠ​ዊ​ያ​ውም ፊት መዘ​ም​ራ​ንን መደበ፤ የቃ​ላ​ቸ​ውም ዜማ ያማ​ረና የጣ​ፈጠ ነበር።

10 መል​ካም በዓ​ል​ንም አደ​ረገ፤ ዓመ​ቱን ሁሉ ደስ አሰኘ፥ ቅዱስ ስሙ​ንም አመ​ሰ​ገ​ነው፤ ቅድ​ስ​ና​ውም ከነ​ግህ ጀምሮ ይነ​ገ​ራል።

11 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ኀጢ​አ​ቱን አስ​ተ​ሰ​ረ​የ​ለት፤ ቀን​ዱ​ንም ለዘ​ለ​ዓ​ለሙ ከፍ ከፍ አደ​ረ​ገ​ለት፤ የተ​ባ​ረ​ከች መን​ግ​ሥ​ትን፥ የእ​ስ​ራ​ኤ​ል​ንም የክ​ብር ዙፋን ሰጠው።


ስለ ንጉሥ ሰሎ​ሞን

12 ከእ​ር​ሱም በኋላ ጠቢብ የሆነ ልጁ ተተ​ካ​ለት ስለ እር​ሱም በስ​ፋት ኖረ።

13 ሰሎ​ሞ​ንም በሰ​ላም ዘመን ነገሠ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በዙ​ሪ​ያው ካሉት ሁሉ አሳ​ረ​ፈው፤ በስሙ ቤትን ሠራ፤ የዘ​ለ​ዓ​ለም መቅ​ደ​ሱ​ንም አዘ​ጋጀ።

14 ሰሎ​ሞን ሆይ፥ ከሕ​ፃ​ን​ነ​ትህ ጀምሮ ጥበ​ብህ እን​ዴት በዛ፤ ማስ​ተ​ዋ​ል​ህም እንደ ፈሳሽ ውኃ ሞላ።

15 ጥበ​ብህ ምድ​ርን ሸፈ​ነ​ቻት፥ ምሳ​ሌ​ህን፥ የነ​ገ​ር​ህ​ንም ትር​ጓሜ አበ​ዛህ።

16 ስም​ህም እስከ ሩቅ ደሴት ድረስ ተሰማ፤ ስለ ሰላ​ም​ህም ተወ​ደ​ድህ።

17 ሀገ​ሮ​ችም ስለ መዝ​ሙ​ርህ፥ ስለ ምሳ​ሌህ፥ ስለ እን​ቆ​ቅ​ል​ሾ​ች​ህና ስለ ትር​ጓ​ሜ​ዎ​ችህ አደ​ነ​ቁህ።

18 የእ​ስ​ራ​ኤል አም​ላክ በተ​ባለ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ስም፥ ወር​ቁ​ንም እንደ እር​ሳስ አደ​ለ​ብ​ኸው፤ ብር​ንም እንደ ማዕ​ድን ቅል​ቅል መላ​ኸው።

19 ሴቶች ልቡ​ና​ህን ለወ​ጡት፤ በሥ​ጋ​ህም ሠለ​ጠ​ኑ​ብህ።

20 ክብ​ር​ህን አስ​ነ​ቀ​ፍህ፤ ዘር​ህ​ንም አሳ​ደ​ፍኽ፤ በል​ጆ​ች​ህም ላይ መቅ​ሠ​ፍ​ት​ንና ጥፋ​ትን አመ​ጣህ፤ ስን​ፍ​ና​ህም አስ​ደ​ነ​ገ​ጠኝ።

21 መን​ግ​ሥ​ት​ህም ተከ​ፈለ፤ ዐመ​ፀኛ መን​ግ​ሥ​ትም ከኤ​ፍ​ሬም ወጣች።

22 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ግን ቸር​ነ​ቱን አል​ተ​ወም፤ ሥራ​ው​ንም አላ​ጠ​ፋም፤ የጻ​ድ​ቃ​ኑ​ንም ልጆች አል​ደ​መ​ሰ​ሰም፤ የሚ​ወ​ዱ​ት​ንም ሰዎች ዘር አላ​ጠ​ፋም፤ ለያ​ዕ​ቆ​ብም ቅሬ​ትን ሰጠው፥ ከእ​ር​ሱም ለዳ​ዊት ሥርን ሰጠው።


ሮብ​አ​ምና ኢዮ​ር​ብ​አም

23 ሰሎ​ሞ​ንም እንደ አባ​ቶቹ አረፈ ከእ​ር​ሱም በኋላ አእ​ምሮ የሌ​ለው ልጁን ለእ​ስ​ራ​ኤል ተወ። ይኸ​ውም ሕዝ​ቡን በም​ክሩ ያሳ​መ​ፃ​ቸው ሮብ​ዓም ነው። እስ​ራ​ኤ​ልን ያሳ​ታ​ቸው፥ ለኤ​ፍ​ሬ​ምም የኀ​ጢ​አት መን​ገ​ድን ያሳየ የና​ባጥ ልጅ ኢዮ​ር​ብ​ዓም ነበረ።

24 ኀጢ​አ​ታ​ቸ​ውም ፈጽሞ በዛ፥ ከሀ​ገ​ራ​ቸ​ውም አስ​ወ​ጥቶ ሰደ​ዳ​ቸው።

25 ፍዳ​ቸ​ውም እስ​ክ​ት​ደ​ር​ስ​ባ​ቸው ድረስ ኀጢ​አ​ትን ሁሉ ፈለ​ጓት።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች