Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽሐፈ ሲራክ 42 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 ነገር ግን ስለ​ዚህ ነገር አት​ፈር፤ ስለ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ሕግ በደል እን​ዳ​ይ​ሆ​ን​ብህ የሰው ፊት አይ​ተህ አታ​ዳላ፤

2 ስለ ልዑል ሕግና ስለ ቃል ኪዳኑ አት​ፈር፤ በደ​ለ​ኛ​ው​ንም እን​ዳ​ታ​ነ​ጻው ስለ ፍርድ አት​ፈር።

3 ከጓ​ደ​ኛህ ጋር ገን​ዘ​ብ​ህን በተ​ሳ​ሰ​ብህ ጊዜ አት​ፈር፤ ስለ ዋጋ​ህና ስለ ርስ​ትህ አት​ፈር።

4 ስለ ሚዛ​ንና ስለ ላዳ​ንም ጥቂት ቢሆን፥ ብዙም ቢሆን ስለ ገን​ዘ​ብህ አት​ፈር።

5 ስለ​ሚ​ረ​ባ​ህና ስለ​ሚ​ጠ​ቅ​ም​ህም ሁሉ አት​ፈር፤ ልጆ​ች​ህ​ንም ስለ ማስ​ተ​ማር አት​ፈር፤ ክፉ ባሪ​ያ​ንም ጎን ጎኑን ግረ​ፈው።

6 በክፉ ሴት ላይ ቍልፍ መያዝ መል​ካም ነው፤ ብዙ እጆች ካሉ​በት ዘን​ድም በቍ​ልፍ አኑር።

7 የም​ት​ሠ​ራ​ውን ሁሉ በቍ​ጥር፥ በመ​ስ​ፈ​ሪ​ያና በሚ​ዛን አድ​ርግ፤ ያገ​ባ​ኸ​ውና ያወ​ጣ​ኸው፥ የሰ​ጠ​ኸ​ውና የተ​ቀ​በ​ል​ኸው ሁሉ በጽ​ሑፍ ይሁ​ንህ።

8 ሰነ​ፍን ሰው፥ አእ​ምሮ የሌ​ለ​ው​ንም ሰው፥ በእ​ር​ጅ​ና​ውም ወደ ዝሙት የሚ​ሄድ ሽማ​ግ​ሌን ስለ መም​ከር አት​ፈር፤ ስለ​ዚህ በሰው ሁሉ ዘንድ በእ​ው​ነት ብል​ህና ዐዋቂ ትሆ​ና​ለህ።

9 ሴት ልጅ ለአ​ባ​ትዋ ስውር የእ​ን​ቅ​ልፍ ዕጦት ናት፤ የወ​ጣ​ት​ነት ዕድ​ሜዋ እን​ዳ​ያ​ል​ፍ​ባት፥ ከተ​ዳ​ረ​ችም በኋላ እን​ዳ​ት​ጠላ፥ ስለ እር​ስዋ ማሰብ ዕን​ቅ​ል​ፍን ያሳ​ጣ​ዋል፤

10 በድ​ን​ግ​ል​ናዋ እን​ዳ​ት​ደ​ፈር፥ በአ​ባ​ቷም ቤት ፀንሳ እን​ዳ​ት​ገኝ፥ ምን​አ​ል​ባ​ትም ከባ​ልዋ ጋር ሳለች እን​ዳ​ት​በ​ድል፥ ካገ​ባ​ችም በኋላ መካን እን​ዳ​ት​ሆን፥

11 የጠ​ላት መዘ​ባ​በቻ፥ በከ​ተ​ማም መነ​ጋ​ገ​ሪያ፥ በሕ​ዝ​ቡም መካ​ከል መሰ​ደ​ቢያ እን​ዳ​ታ​ደ​ር​ግህ፥ በብዙ ሰዎች ፊትም እን​ዳ​ታ​ሳ​ፍ​ርህ የማ​ታ​ፍር ልጅን አጽ​ን​ተህ ጠብ​ቃት።

12 ለሰው ሁሉ ስለ መልኩ አታ​ድ​ላ​ለት፤ በሴ​ቶ​ችም መካ​ከል አት​ግባ፤

13 ከል​ብስ ብል ይገ​ኛል፤ ክፋ​ትም ሁሉ ከሴ​ቶች ይገ​ኛል።

14 ኀፍ​ረ​ት​ንና ቅን​ዐ​ትን ከም​ታ​መጣ ሴት ደግ​ነት፤ የወ​ንድ ክፋት ይሻ​ላል።


የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ክብር በፍ​ጥ​ረቱ

15 እን​ግ​ዲህ ወዲህ ግን የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ሥራ አስ​ባ​ለሁ፤ ያየ​ሁ​ት​ንም እና​ገ​ራ​ለሁ፤ ፍጥ​ረት ሁሉ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቃል ተፈ​ጥ​ሯ​ልና።

16 ፀሐይ ያበ​ራል፤ ሁሉ​ንም ያሳ​ያል፤ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ጌት​ነት በሥ​ራው ሁሉ ላይ ምሉእ ነው።

17 ሁሉ በክ​ብሩ ይጸና ዘንድ፥ ሁሉን ቻይ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ያጸ​ና​ውን አላ​ደ​ረ​ገ​ምን?

18 ጥል​ቅ​ንና ልብን መር​ምሮ ያው​ቃ​ቸ​ዋል፤ ምክ​ራ​ቸ​ው​ንም ሁሉ ያው​ቃል፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የል​ቡና አሳ​ብን ሁሉ ያው​ቃል፤ የዓ​ለ​ም​ንም ምል​ክት ያያል።

19 ያለ​ፈ​ው​ንም፥ የሚ​መ​ጣ​ው​ንም እርሱ ይና​ገ​ራል፤ የተ​ሰ​ወ​ረ​ው​ንም ፍለጋ ይገ​ል​ጣል።

20 ከም​ክ​ርም ሁሉ የሚ​ያ​መ​ል​ጠው የለም፤ ከነ​ገሩ ሁሉ አንድ ቃል ስንኳ የሚ​ሰ​ወ​ረው የለም።

21 የጥ​በ​ቡን ገና​ና​ነት አስ​ጌጠ። ይህ​ቺም ዓለም ሳይ​ፈ​ጠር የነ​በ​ረች ናት፥ ለዘ​ለ​ዓ​ለ​ሙም ትኖ​ራ​ለች፤ አት​ጨ​ም​ርም፤ አት​ጐ​ድ​ል​ምም፤ አንድ መካ​ርን ስንኳ አይ​ፈ​ል​ግም።

22 ሥራው ሁሉ ያማረ ነው፤ ለማ​የ​ትም እንደ ብር​ሃን ነው፤

23 ይህ ሁሉ ለዘ​ለ​ዓ​ለም ሕያው ሆኖ ይኖ​ራል፤ ለጥ​ቅም በሚ​ፈ​ል​ጉት ጊዜ ይሰ​ማል።

24 ሁሉም አንዱ የሌ​ላው ተቃ​ራኒ በመ​ሆን ሁለት ሁለት ናቸው፤ ምንም ነጠላ አድ​ርጎ የፈ​ጠ​ረው የለም።

25 ለመ​ል​ካም ነገር አን​ዱን ከሁ​ለ​ተ​ኛው ጋር አጸ​ናው፤ ክብ​ሩን ከማ​የት ማን ይጠ​ግ​ባል?

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች