Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽሐፈ ሲራክ 38 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ባለ መድ​ኀ​ኒ​ትና መድ​ኀ​ኒት

1 ባለ መድ​ኀ​ኒ​ትን አክ​ብ​ረው፥ እንደ እጁ እን​ዲሁ ክብሩ ነውና። እር​ሱ​ንም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፈጥ​ሮ​ታ​ልና።

2 ማዳን ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የሚ​ገኝ ሲሆን፥ ክብ​ርን ግን ከን​ጉሥ ይቀ​በ​ላል።

3 ሰው ሁሉ ባለ መድ​ኀ​ኒ​ትን በጥ​በቡ ያከ​ብ​ረ​ዋል፤ በመ​ኳ​ን​ን​ትም ዘንድ ይመ​ሰ​ገ​ናል።

4 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መድ​ኀ​ኒ​ትን ከም​ድር ፈጠረ፤ ጠቢብ ሰውም ይህን አይ​ን​ቀ​ውም።

5 ኀይ​ሉን ያውቁ ዘንድ፥ ውኃ በእ​ን​ጨት የጣ​ፈጠ አይ​ደ​ለ​ምን?

6 በጌ​ት​ነቱ ይከ​ብሩ ዘንድ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ለሰ​ዎች ጥበ​ብን ሰጣ​ቸው።

7 በመ​ድ​ኀ​ኒቱ ያድ​ና​ቸ​ዋል፤ በሽ​ታ​ቸ​ው​ንም ያር​ቅ​ላ​ቸ​ዋል።

8 ያድኑ ዘንድ ከእ​ነ​ርሱ መድ​ኀ​ኒ​ትን ያደ​ር​ጋሉ፤ እር​ሱም ለሀ​ገር ሰላ​ምን ያመ​ጣል።

9 ልጄ ሆይ፥ በሽ​ታ​ህን ቸል አት​በል፤ ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ጸልይ፤ እር​ሱም ይፈ​ው​ስ​ሃል።

10 ኀጢ​አ​ትን ተዋት፤ እጅ​ህን አቅና፤ ልቡ​ና​ህ​ንም ከኀ​ጢ​አት ሁሉ አንጻ።

11 መባ​እ​ህን አግባ፤ የመ​ታ​ሰ​ቢ​ያ​ው​ንም የስ​ንዴ ዱቄት ስጥ፤ የሰባ መሥ​ዋ​ዕ​ት​ህ​ንም የተ​ቻ​ለ​ህን ያህል አብ​ዝ​ተህ አቅ​ርብ፤

12 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እር​ሱን ፈጥ​ሮ​ታ​ልና፤ ለባለ መድ​ኀ​ኒት መን​ገ​ድን አብ​ጅ​ለት፥ እር​ሱ​ንም ትሻ​ዋ​ለ​ህና ከአ​ንተ አታ​ር​ቀው።

13 በእ​ጃ​ቸው ፈውስ የሚ​ደ​ረ​ግ​በት ጊዜ አለና።

14 ይረ​ዳ​ቸው ዘንድ፥ ዕረ​ፍ​ት​ንም ይሰ​ጣ​ቸው ዘንድ፥ ሁል​ጊ​ዜም ይፈ​ው​ሳ​ቸው ዘንድ እነ​ርሱ ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይለ​ም​ናሉ።

15 ፈጣ​ሪ​ውን የሚ​በ​ድል በባለ መድ​ኀ​ኒት እጅ ይወ​ድ​ቃል።


ለሞተ ሰው መታ​ሰ​ቢያ ስለ ማድ​ረግ

16 ልጄ ሆይ፥ ለሞተ ሰው አል​ቅ​ስ​ለት፥ እዘ​ን​ለ​ትም፤ ራስ​ህ​ንም አሳ​ዝን፤ እንደ ሥር​ዐ​ቱም መታ​ሰ​ቢያ አድ​ር​ግ​ለት። ያገ​ለ​ገ​ለ​ህን ሰው ሞት ቸል አት​በል።

17 እንደ ልማዱ መራራ ልቅሶ አል​ቅ​ስ​ለት፤ ጥልቅ ኀዘ​ንም እዘ​ን​ለት፥ የኀ​ዘን መዝ​ሙ​ርም ዘም​ር​ለት፤ እንደ ሕጉም አንድ ቀን ቢሆን ሁለት ቀን ቢሆን አል​ቅ​ስ​ለት።

18 ከዚህ በኋላ ልቅ​ሶ​ህን ተው። ኀዘ​ንም አይ​ግ​ባህ፤ በኀ​ዘን የሞቱ ብዙ​ዎች ናቸ​ውና፥ የልብ ኀዘ​ንም ኀይ​ልን ይሰ​ብ​ራ​ልና።

19 ኀዘ​ንና ትካዜ ለሞት ያደ​ር​ሳል፤ የድ​ሃም ዘመኑ ሁሉ በኀ​ዘን ያል​ቃል።

20 ኀዘ​ንን ወደ ልቡ​ናህ አታ​ግባ፤ ኀዘ​ንን ከአ​ንተ አር​ቃት።

21 ድኅ​ነት እን​ደ​ሌ​ለ​ባት ዕወቅ፤ ራስ​ህ​ንም ትጎ​ዳ​ለህ፥ ታሳ​ዝ​ና​ለህ፥ የም​ት​ጠ​ቅ​መ​ውም ነገር የለም።

22 እኔ የተ​ቀ​በ​ል​ሁ​ትን ፍዳ አስ​ተ​ውል፤ አን​ተም እን​ደ​ዚሁ ፍዳን እን​ደ​ም​ት​ቀ​በል ዕወቅ። እኔ ዛሬ አን​ተም ነገ።

23 የሞተ ሰውስ ዐረፈ፤ ነገር ግን መታ​ሰ​ቢ​ያ​ውን አድ​ር​ግ​ለት፤ ከዚህ በኋላ ነፍሱ ታርፍ ዘንድ ልቅ​ሶ​ህን ተው።

24 የጸ​ሓፊ ጥበቡ በተ​ሾ​መ​በት ወራት ነው፤ ሥራ​ውን የማ​ያ​በዛ ሰው አይ​ራ​ቀ​ቅም።

25 ዕር​ፉን የሚ​ያ​ጸና ሰው በም​ንም አይ​ራ​ቀ​ቅም፥ በእ​ር​ሻው ይታ​በ​ያል፥ በሬ​ው​ንም ይገ​ር​ፋል፤ በሥ​ራ​ውም ይመ​ላ​ለ​ሳል፤ ነገ​ሩም ሁሉ ስለ በሬና ወይ​ፈን ነው።

26 አሳቡ እር​ሻ​ውን እን​ዲ​ያ​ርስ ነው፤ ትጋ​ቱም በሬ​ውን ገለባ ያበላ ዘንድ ነው፤ ወይ​ፈ​ኑ​ንም እስ​ኪ​ያ​ቀና ድረስ ይደ​ክ​ማል።

27 ሌሊቱ ቀን የሚ​ሆ​ን​ባ​ቸው ጠራ​ቢና የጠ​ራ​ቢ​ዎች አለቃ፥ የማ​ኅ​ተም ቅርጽ የሚ​ቀ​ር​ጹና የሚ​ያ​ለ​ዝቡ ሰዎች እንደ እርሱ ናቸው፤ እነ​ዚ​ህም አሳ​ባ​ቸው ሁሉ በየ​መ​ልኩ መስ​ለው ይሠሩ ዘንድ ነው፤ ምክ​ራ​ቸ​ውም ሁሉ ማኅ​ተ​ሙን ማለ​ዘ​ብን ይጠ​ነ​ቀቁ ዘንድ ነው፤ ትጋ​ታ​ቸ​ውም ሥራ​ቸ​ውን ይፈ​ጽሙ ዘንድ ነው።

28 በወ​ናፍ አጠ​ገብ የሚ​ቀ​መጥ፥ የብ​ረ​ት​ንም ሥራ የሚ​ማር አን​ጥ​ረኛ እንደ እርሱ ነው። የወ​ና​ፉም ጢስ ሰው​ነ​ቱን ያሻ​ክ​ረ​ዋል። እሳ​ቱም ሰው​ነ​ቱን ያቀ​ል​ጣ​ታል፤ የመ​ዶ​ሻ​ውም ድምፅ ጆሮ​ውን ያደ​ነ​ቍ​ረ​ዋል። ዐይ​ኖ​ቹም ወደ መሣ​ሪ​ያው ይመ​ለ​ከ​ታሉ፤ በል​ቡም ሥራ​ውን ይጨ​ርስ ዘንድ ያስ​ባል፤ ትጋ​ቱም መሣ​ሪ​ያ​ው​ንና ወና​ፉን ያሳ​ምር ዘንድ ነው።

29 በሥ​ራው የሚ​ቀ​መጥ ሸክላ ሠሪም እንደ እርሱ ነው፥ በእ​ግ​ሩም መን​ኰ​ራ​ኵ​ርን ያዞ​ራል፤ ሥራ​ው​ንም እን​ዴት እን​ደ​ሚ​ፈ​ጽም ሁል​ጊዜ ያስ​ባል። የሠ​ራ​ው​ንም ሁሉ ይቈ​ጥ​ራል።

30 በእ​ጁም ጭቃ​ውን መስሎ ይሠ​ራል፤ በእ​ግሩ ጭቃ​ውን ሲረ​ግጥ ኀይ​ሉን ያደ​ክ​ማል፤ የል​ቡ​ና​ውም አሳብ ሥራ​ውን ይጨ​ርስ ዘንድ ነው። ትጋ​ቱም መወ​ል​ወ​ያ​ውን ያዞር ዘንድ ነው።

31 እነ​ዚህ ሁሉ የእ​ጃ​ቸ​ውን ሥራ ተስፋ ያደ​ር​ጋሉ፤ ሁሉም በሥ​ራ​ቸው ይራ​ቀ​ቃሉ።

32 ያለ እነ​ር​ሱም ሀገር መኖር አት​ች​ልም።

33 ነገር ግን በሸ​ንጎ ምክ​ርን አያ​ስ​መ​ክ​ሯ​ቸ​ውም፤ በአ​ደ​ባ​ባ​ይም ከመ​ኳ​ን​ንት ጋራ አያ​ስ​ቀ​ም​ጧ​ቸ​ውም፤ የቅ​ጣት ፍር​ድ​ንም አያ​ስ​ፈ​ር​ዷ​ቸ​ውም፤ አያ​ስ​ገ​ዟ​ቸ​ውም፤ አያ​ሠ​ለ​ጥ​ኗ​ቸ​ው​ምም።

34 ነገ​ርን መስሎ በመ​ና​ገር አይ​ኖ​ሩም፤ ነገር ግን ያገ​ርን ፈቃድ ያጸ​ናሉ፤ ጸሎ​ታ​ቸ​ውም በሥ​ራ​ቸው ይራ​ቀቁ ዘንድ ነው።

35 ዕው​ቀት ግን በልቡ ለሚ​ተጋ ሰው ነው። የል​ዑ​ል​ንም ሕግ ለሚ​ያ​ስብ ሰው ነው።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች