Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽሐፈ ሲራክ 37 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 ወዳጅ ያበጀ ሰው ሁሉ እኔም ወዳጁ ነኝ ይላል፤ ነገር ግን በከ​ንቱ ለስም ወዳጅ የሚ​ሆን ሰው አለ።

2 በል​ቡ​ናው ግን እስ​ከ​ሚ​ሞ​ት​በት ቀን ድረስ ኀዘን ይኖ​ራል፤ ጠላት የሚ​ሆን ወዳ​ጅም አለ።

3 ክፉ ምኞት ሆይ! ከወ​ዴት ተገ​ኘሽ፤ በም​ድሩ ሁሉ ኀጢ​አ​ትን መላሽ።

4 በደ​ስ​ታህ ጊዜ የሚ​ቀ​ር​ብህ ወዳጅ አለ፤ ብት​ቸ​ገር ግን እርሱ ጠላት ይሆ​ን​ሃል።

5 በበ​ሽ​ታህ ጊዜ ስለ ሆዱ የሚ​ያ​ዝ​ን​ልህ ወዳጅ አለ፤ የሚ​ከ​ዳህ ሰው ቢኖር ግን ይገ​ድ​ልህ ዘንድ እርሱ ይቀ​ድ​ማል።

6 በተ​መ​ቸህ ጊዜ ወዳ​ጅ​ህን አት​ርሳ፤ ገን​ዘ​ብም ብታ​ገኝ አት​ተ​ወው።

7 መካር ሁሉ ምክ​ርን ይመ​ክ​ራል፤ ነገር ግን ራሱን ይጠ​ቅም ዘንድ የሚ​መ​ክር ሰው አለ።

8 ከሚ​መ​ክ​ርህ ሰው ልቡ​ና​ህን ጠብቅ፤ ስለ ራሱ ይመ​ክ​ር​ሃ​ልና፤ ይወ​ድ​ድ​ህም ዘንድ አስ​ቀ​ድ​መህ ፍላ​ጎ​ቱን ዕወ​ቅ​በት።

9 ገን​ዘ​ብ​ህን የሚ​ያ​ጠ​ፋ​ብ​ህን ነገር ያመ​ጣ​ብ​ሃል በጎ ነገር አደ​ረ​ግህ ይል​ሃል፤ በተ​ቸ​ገ​ር​ህም ጊዜ አይቶ ይስ​ቅ​ብ​ሃል።

10 ከሚ​ጠ​ባ​በ​ቅህ ሰው ጋራ አት​ማ​ከር፤ ከሚ​መ​ቀ​ኝ​ህም ሰው ነገ​ር​ህን ሰውር።

11 ከሴት ጋር ስለ​ሚ​ያ​ስ​ቀ​ናት ነገር አት​ና​ገር፤ ስለ ጦር​ነ​ትም ከፈሪ ሰው ጋር አት​ማ​ከር። ስለ ትር​ፍም ከሻጭ ጋር አት​ማ​ከር፤ ስለ ንግድ ነገ​ርም ከነ​ጋዴ ጋር አት​ማ​ከር። ስለ ምጽ​ዋ​ትም ከን​ፉግ ሰው ጋር አት​ማ​ከር። ዋጋን ስለ መመ​ለ​ስም ከከ​ዳ​ተኛ ጋር አት​ማ​ከር፤ ስለ ሥራም ከሰ​ነፍ ሰው ጋራ አት​ማ​ከር፤ ሥራ ስለ​ሚ​ፈ​ጸ​ም​በት ዓመ​ትም ከም​ን​ደኛ ጋር አት​ማ​ከር። ስለ ጥበ​ብም ከአ​ላ​ዋቂ ሰው ጋር አት​ማ​ከር፤ ከዚ​ህም ሁሉ ጋር ስለ​ዚህ ነገር የም​ት​ማ​ከ​ረው አይ​ኑር።

12 ሃይ​ማ​ኖት እን​ዳ​ለው ከም​ታ​ው​ቀው፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ከሚ​ፈራ፥ ልቡ​ና​ውም እንደ ልብህ ከሆነ ጻድቅ ሰው ጋር ምክ​ር​ህን ተና​ገር፤ ብታ​ዝ​ንም ከአ​ንተ ጋር ያዝ​ናል።

13 እር​ስዋ ከሁሉ ይልቅ ታማ​ኝህ ናትና፤ የል​ቡ​ና​ህን ምክር አጽና።

14 የሰው ልቡና ከሰ​ባት ጠባ​ቂ​ዎች ይልቅ የሚ​ደ​ር​ስ​በ​ትን ነገር ፈጽማ ታስ​ታ​ው​ቀ​ዋ​ለ​ችና።

15 ከዚህ ሁሉ ጋር መን​ገ​ድ​ህን በእ​ው​ነት ያቀ​ና​ልህ ዘንድ፥ ወደ ልዑል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ለምን።

16 የመ​ፍ​ቅድ ሁሉ መጀ​መ​ሪያ ቃል ነው፤ የሥ​ራም ሁሉ መጀ​መ​ሪያ ምክር ነው።

17 የሰው የልቡ ምል​ክት በአ​ራቱ ወገን ይታ​ያል።

18 እነ​ዚ​ህም ኀዘ​ንና ደስታ ሞትና ሕይ​ወት ናቸው። እነ​ዚ​ህ​ንም ሁሉ አን​ደ​በት ያመ​ጣ​ቸ​ዋል።

19 ሁሉን የሚ​ማር፥ ብዙም የሚ​ያ​ውቅ ሰው አለ፤ ነገር ግን ሰው​ነ​ቱን መጥ​ቀም አይ​ች​ልም።

20 በነ​ገር የሚ​ራ​ቀቅ፥ ነገር ግን ራሱን የሚ​ያ​ስ​ጠላ ሰው አለ። እን​ደ​ዚህ ያለ​ውን ሰው ጥቅሙ ሁሉ ያል​ፈ​ዋል።

21 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሞገ​ስን አይ​ሰ​ጠ​ው​ምና ከጥ​በ​ቡም ሁሉ ወጥ​ት​ዋ​ልና።

22 በራሱ የሚ​ራ​ቀቅ፥ በቃ​ሉም የዋህ የሚ​ሆን ሰው አለ።

23 ብልህ ሰው ወገ​ኖ​ቹን ይመ​ክ​ራ​ቸ​ዋል፤ ለዘ​መ​ዶ​ቹም ጥበ​ብን ያስ​ተ​ም​ራ​ቸ​ዋል።

24 ብልህ ሰው በበ​ረ​ከት ይጠ​ግ​ባል፤ ያዩ​ትም ሰዎች ሁሉ ብፁዕ ይሉ​ታል።

25 የሰው ዘመኑ በቍ​ጥር ነው፤ የእ​ስ​ራ​ኤል ዘመን ግን የማ​ይ​ቈ​ጠር ነው።

26 ለወ​ገ​ኖቹ ጥበ​በኛ የሆነ ሰው ዋጋ​ውን ያገ​ኛል፤ ስሙም ለዘ​ለ​ዓ​ለም ይኖ​ራል።

27 ልጄ ሆይ፥ በሕ​ይ​ወት ሳለህ ሰው​ነ​ት​ህን ፈት​ናት፥ የሚ​ጎ​ዳ​ት​ንም ዐው​ቀህ አት​ስ​ጣት፤

28 ሁሉ ለሰ​ው​ነት የሚ​ገ​ባት አይ​ደ​ለ​ምና፥ ሁሉም ደስ የሚ​ያ​ሰ​ኛት አይ​ደ​ለ​ምና፤

29 ለመ​ብል ሁሉ አት​ሰ​ስት፤ ላየ​ኸ​ውም እህል ሁሉ አት​ሳሳ።

30 ብዙ መብ​ላት ደዌ ይሆ​ና​ልና፤ ስስ​ትም ጓታን ያበ​ዛ​ዋ​ልና።

31 ስስት የገ​ደ​ላ​ቸው ሰዎች ብዙ ናቸው፥ መጥኖ የሚ​በላ ሰው ግን ሰው​ነቱ ጤነኛ ነው።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች