Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽሐፈ ሲራክ 35 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 አለ​ቃም አድ​ር​ገው ቢሾ​ሙህ ራስ​ህን አታ​ኵራ፤ ከእ​ነ​ርሱ እንደ አንዱ ሁን፤ ኀዘ​ና​ቸ​ው​ንም እዘን፤ ተቀ​ም​ጠ​ህም ፍረ​ድ​ላ​ቸው።

2 ሥራ​ህን ጨር​ሰህ ዕረፍ፤ መል​እ​ክ​ት​ህን ጨር​ሰህ የክ​ብር ዘው​ድን ታገኝ ዘንድ ከእ​ነ​ርሱ ጋራ ደስ ይበ​ልህ።

3 ሽማ​ግሌ ሆይ፥ ተና​ገር፤ ይገ​ባ​ሃ​ልም፥ ለበጎ ነገ​ርም ቸል አት​በል፤ የጥ​በ​ብ​ህ​ንም ነገር ተና​ገር።

4 ለመ​ረ​መ​ረህ ሰው ሁሉ ቃል​ህን አት​ና​ገር፤ እን​ዳ​ገ​ኘ​ህም አት​ራ​ቀቅ።

5 በወ​ርቅ ጌጥ ክቡር ዕንቍ ደስ እን​ደ​ሚ​ያ​ሰኝ፥ ዘፈ​ንም ወይን በሚ​ጠጡ ሰዎች ዘንድ እን​ዲሁ ነው።

6 በወ​ርቅ ዝር​ግፍ ላይ ዕንቍ እን​ደ​ሚ​ያ​ምር፤ ዘፈ​ንና መሰ​ንቆ በመ​ጠጥ ቤት እን​ዲሁ ያማረ ነው።

7 ጎል​ማሳ! ከተ​ፈ​ቀ​ደ​ልህ ተና​ገር፤ ዳግ​መ​ኛም ቢጠ​ይ​ቁህ በጭ​ንቅ ተና​ገር።

8 አንድ ጊዜ ተና​ግ​ረህ፥ ወዲ​ያ​ውኑ ነገ​ር​ህን ጨርስ፤ እያ​ወ​ቅ​ህም በአ​ን​ደ​በ​ትህ ዝም በል።

9 በታ​ላ​ላ​ቆች መካ​ከል አት​ቀ​መጥ፤ ሌላ ሰውም ሲና​ገር ነገ​ር​ህን አት​ና​ገር።

10 መብ​ረቅ ከነ​ጐ​ድ​ጓድ በፊት እን​ደ​ሚ​ሮጥ፥ እን​ዲሁ የሚ​ያ​ፍር ሰው መከ​በሩ በፊቱ ነው።

11 ወደ ቤትህ ገብ​ተህ ሁሉን በጊ​ዜው መጥ​ነህ አድ​ርግ፤ በዚ​ያም ደስ ይበ​ልህ ተጫ​ወ​ትም።

12 የሚ​ገ​ባ​ው​ንና የሚ​ወ​ደ​ደ​ው​ንም ሁሉ አድ​ርግ፤ የት​ዕ​ቢ​ትን ነገር እን​ዳ​ት​ና​ገር ዕወቅ፤ በቃ​ል​ህም አት​በ​ድል።

13 ከዚህ ሁሉ ጋራ ፈጣ​ሪ​ህን አመ​ስ​ግ​ነው፤ እር​ሱም ከበ​ረ​ከቱ ሁሉ ያጠ​ግ​ብ​ሃል።


ሕግን መተ​ር​ጐም

14 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የሚ​ፈራ ሰው ለሕጉ ይገ​ዛል፤ ወደ እር​ሱም ፈጥ​ነው የሚ​ሄዱ ሰዎች መፍ​ቅ​ዳ​ቸ​ውን ያገ​ኛሉ።

15 ሕጉ​ንም የሚ​ፈ​ል​ገው ከእ​ርሱ ይጠ​ግ​ባል፤ በእ​ርሱ የሚ​ጠ​ራ​ጠር ግን ይወ​ድ​ቃል፤ ይበ​ድ​ላ​ልም።

16 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የሚ​ፈ​ሩት ሰዎች ፍር​ድን ያገ​ኛሉ፤ በእ​ኩለ ቀንም ተበ​ቅሎ ጠላ​ቶ​ቻ​ቸ​ውን ያጠ​ፋ​ላ​ቸ​ዋል።

17 ኀጢ​አ​ተኛ ሰው ግን የሚ​መ​ክ​ሩ​ትን አይ​ሰ​ማም፤ ሁሉም እንደ እርሱ ይመ​ስ​ለ​ዋል።

18 ብልህ ሰው ያለ ምክር የሚ​ሠ​ራው ሥራ የለም፤ የሚ​ሠ​ራ​ውም ሥራ የበጀ ይሆ​ን​ለ​ታል፤ ፍር​ሀ​ትን የማ​ያ​ስብ ትዕ​ቢ​ተኛ ጠላት ግን ያለ ምክር ይሠ​ራል።

19 ልጄ ሆይ፥ አንተ ግን ያለ ምክር የም​ት​ሠ​ራው ሥራ አይ​ኑር፤ የሠ​ራ​ኸ​ው​ንም ሥራ አታ​ጥፋ።

20 በጥ​ፋት ድን​ጋይ እን​ዳ​ት​ሰ​ነ​ካ​ከል፥ መን​ገድ በሌ​ለ​በት በም​ድረ በዳ አት​ሂድ።

21 ጠላ​ት​ህን በም​ድረ በዳ አት​መ​ነው።

22 በፈ​ቃ​ድህ የማ​ይ​ሄድ ልጅ​ህን ስንኳ አት​መ​ነው።

23 በሠ​ራ​ኸው ሥራ ሁሉ ሰው​ነ​ት​ህን ደስ አሰ​ኛት፥ በሁ​ሉም ትእ​ዛ​ዙን ጠብቅ።

24 ሕጉን የሚ​ጠ​ብቅ ሰው የመ​ጽ​ሓ​ፉን ትእ​ዛዝ ይሰ​ማል፤ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም የሚ​ያ​ምን ሰው የሚ​ያ​ጣው ነገር የለም።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች