Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽሐፈ ሲራክ 29 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ስለ ማበ​ደ​ርና መበ​ደር

1 ምጽ​ዋ​ትን የሚ​መ​ጸ​ውት ሰው ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ያበ​ድ​ራል፤ በእ​ጁም የሚ​በቃ ያለው ትእ​ዛ​ዙን ይፈ​ጽ​ማል።

2 በደ​ስ​ታው ጊዜ ከእ​ርሱ ጋር ደስ ይልህ ዘንድ፥ በተ​ቸ​ገረ ጊዜ ለባ​ል​ን​ጀ​ራህ አበ​ድ​ረው።

3 ቃል​ህን ጠብቅ፤ ከእ​ር​ሱም ጋራ ተማ​መን፤ በጊ​ዜ​ውም የሚ​ያ​ስ​ፈ​ል​ግ​ህን ነገር ታገ​ኛ​ለህ።

4 የብ​ድ​ርን ገን​ዘብ በም​ድር ላይ ወድቆ ያገ​ኙት የሚ​መ​ስ​ላ​ቸው ብዙ​ዎች ናቸው፤ የረ​ዷ​ቸ​ው​ንና ያበ​ደ​ሩ​አ​ቸ​ው​ንም ችግር ይፈ​ጥ​ሩ​ባ​ቸ​ዋል።

5 እስ​ኪ​በ​ደ​ርህ ድረስ ራስ​ህን ይስ​ም​ሃል፤ ቃሉ​ንም ያለ​ሰ​ል​ሳል፤ ገን​ዘ​ብ​ህ​ንም እስ​ኪ​ወ​ስድ ድረስ ያባ​ብ​ል​ሃል፤ በሚ​ከ​ፍ​ል​በት ጊዜ ግን ቀጠ​ሮ​ህን ያረ​ዝ​ም​ብ​ሃል፤ በገ​ን​ዘ​ብ​ህም ጠብና ክር​ክ​ርን ይከ​ፍ​ል​ሃል፤ ያደ​ክ​ም​ሃል፤ ቀጠ​ሮ​ህ​ንም ያሳ​ል​ፋል።

6 እኩ​ሌ​ታ​ውን ቢከ​ፍ​ልህ በጭ​ንቅ ነው፤ ዳግ​መ​ኛም ያንኑ በም​ድር ላይ ወድቆ ያገ​ኘ​ኸው ይመ​ስ​ል​ሃል፤ ይህስ ካል​ሆነ ገን​ዘ​ብ​ህን ሁሉ ታጣ​ለህ፤ ዳግ​መ​ኛም ጠላት ይሆ​ን​ሃል፤ ርግ​ማ​ን​ንና ስድ​ብን ይከ​ፍ​ል​ሃል፤ ከሚ​ያ​ከ​ብ​ር​ህም ይልቅ ያዋ​ር​ድ​ሃል።

7 ገን​ዘ​ባ​ቸ​ውን እን​ዳ​ያ​ጡና እን​ዳ​ይ​ጣሉ በመ​ፍ​ራ​ትና ጠብን ባለ​መ​ው​ደድ ገን​ዘ​ባ​ቸ​ውን የማ​ያ​በ​ድሩ ሰዎች ብዙ ናቸው።


ስለ ምጽ​ዋት

8 ድሃ​ዉን ግን ታገ​ሠው፤ ምጽ​ዋ​ቱ​ንም ስጠው፤ አል​ፈ​ኸ​ውም አት​ሂድ።

9 ችግ​ረኛ ነውና በሕግ እንደ ታዘ​ዘው ድኃ​ዉን በም​ጽ​ዋት ተቀ​በ​ለው፤ ባዶ​ው​ንም አት​መ​ል​ሰው።

10 ባል​ን​ጀ​ራ​ህ​ንና ወዳ​ጅ​ህን ከም​ታጣ፥ ተቀ​ብሮ ከሚ​ዝ​ግና በድ​ን​ጋ​ይም ሥር ከሚ​ጠፋ ወር​ቅ​ህን እጣ።

11 ስለ ልዑል ትእ​ዛዝ በወ​ር​ቅህ አስ​ተ​ዋ​ፅኦ አድ​ርግ፤ ከወ​ርቅ ድልብ የበ​ለ​ጠም ያተ​ር​ፍ​ል​ሃል።

12 ምጽ​ዋ​ትን በቤ​ቶ​ችህ አድ​ል​ባት፤ እር​ስ​ዋም ትሻ​ላ​ለች፤ ከመ​ከ​ራ​ህም ሁሉ አን​ተን ማዳን ትች​ላ​ለች።


ስለ ዋስ​ትና

13 ከጦ​ርና ጋሻ ትሻ​ላ​ለች፤ ጠላ​ት​ህን ድል ትነ​ሣ​ል​ሃ​ለች፤ ታጠ​ፋ​ል​ሃ​ለ​ችም።

14 ደግ ሰው ጎረ​ቤ​ቱን ይዋ​ሰ​ዋል፤ የማ​ያ​ፍር ሰው ግን ባል​ን​ጀ​ራ​ውን ቸል ይላል።

15 ስለ አንተ ፋንታ ሰው​ነ​ቱን አሳ​ልፎ ሰጥ​ት​ዋ​ልና የተ​ዋ​ሰ​ህን ሰው ውለታ አት​ርሳ።

16 ጠብን ለማ​ጥ​ፋት መዋስ ደግ ነገር ነው።

17 ኀጢ​አ​ተኛ ሰው ግን ያዳ​ነ​ውን ሰው ውለታ ይዘ​ነ​ጋል።

18 መዋስ ብዙ ደጋግ ሰዎ​ችን አሳ​ዘነ፤ እንደ ባሕር ማዕ​በ​ልም አወ​ካ​ቸው፤ አር​በ​ኞች ሰዎ​ች​ንም አሳ​ታ​ቸው፤ ወደ ባዕድ ሕዝ​ብም አሳ​ደ​ዳ​ቸው።

19 ኀጢ​አ​ተኛ ሰው ግን በመ​ዋስ ይጠ​ፋል፤ ለት​ር​ፍም የሚ​ሳሳ ሰው በመ​ከራ ይወ​ድ​ቃል።

20 በተ​ቻ​ለህ መጠን ባል​ን​ጀ​ራ​ህን ርዳው፤ ነገር ግን እን​ዳ​ያ​ስ​ትህ ራስ​ህን ጠብቅ።

21 የሕ​ይ​ወ​ትህ መጀ​መ​ሪያ እህ​ልና ውኃ፥ ልብ​ስም ነው፤ ቤትህ ግን ኀፍ​ረ​ት​ህን የም​ት​ሰ​ው​ር​በት ነው።

22 በሌላ ሰው ገን​ዘብ በባ​ዕድ ቤት ፈጽ​መህ ደስ ከሚ​ልህ፥ በራ​ስህ ጎጆ ብት​ቸ​ገር ይሻ​ል​ሃል።

23 ለታ​ና​ሹም ለታ​ላ​ቁም ሥራ​ህ​ንና ቃል​ህን አሳ​ምር።

24 ካንዱ ቤት ወደ ሌላው ቤት የሚ​ዞር ሰው ኑሮው ክፉ ነው፤ ባደ​ር​ህ​በት ቦታ ክፉ ነገር እን​ዳ​ት​ና​ገር ተጠ​ን​ቀቅ።

25 ያም ባይ​ሆን ታበ​ላ​ለህ፤ ታጠ​ጣ​ለ​ህም፤ ምስ​ጋና ግን አይ​ኖ​ር​ህም፥ ከዚ​ህም ሁሉ ጋር መራራ ነገ​ርን ይመ​ል​ሱ​ል​ሃል።

26 በተ​ዘ​ጋ​ጀህ ጊዜ ግን እን​ዲህ ይሉ​ሃል፥ “እን​ግ​ዳ​ችን ገብ​ተህ ማዕ​ድን ሥራ፤ ያለ​ህ​ንም አብ​ላን።”

27 ብት​ቸ​ገር ግን፥ “እን​ግ​ዳ​ችን ውጣ፤ አማ​ቻ​ችን ደረሰ፤ ቤታ​ች​ንን እን​ፈ​ል​ገ​ዋ​ለን” ይሉ​ሃል።

28 ይህ ነገር በብ​ልህ ሰው ዘንድ ጭንቅ ነው፤ ያሳ​ደ​ር​ኸው ሰው ያዋ​ር​ድ​ሃል፤ ያበ​ደ​ር​ኸ​ውም ሰው ይሰ​ድ​ብ​ሃል።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች