Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ

- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽሐፈ ሲራክ 27 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 በግ​ብ​ዝ​ነት ኀጢ​አ​ትን የሚ​ሠ​ሩ​አት ብዙ​ዎች ናቸው፤ ገን​ዘቡ ይበ​ዛ​ለት ዘንድ የሚ​ወ​ድድ ሰው ግን ዐይ​ኑን ይመ​ል​ሳል።

2 ችን​ካር በድ​ን​ጋይ ግንብ መካ​ከል እን​ደ​ሚ​ተ​ከል፥ በመ​ሸ​ጥና በመ​ግ​ዛት መካ​ከል ኀጢ​አት ትመ​ጣ​ለች።

3 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን በመ​ፍ​ራት ፈጥኖ ካል​ተ​ጠ​በቀ፥ የቤቱ ውድ​ቀት አይ​ዘ​ገ​ይም።


የሕ​ይ​ወት መመ​ዘኛ

4 በወ​ን​ጠ​ፍት ዐሠር ይከ​ማ​ቻል፤ እን​ዲ​ሁም ሁሉ ሰውን ኀጢ​አቱ ታገ​ኘ​ዋ​ለች።

5 የሸ​ክላ ዕቃን እሳት ይፈ​ት​ነ​ዋል፤ ሰው​ንም የል​ቡ​ናው ዐሳብ ይፈ​ት​ነ​ዋል።

6 ተክል የሚ​ጠ​ብቅ ሰው ፍሬ​ውን ያያል፤ እን​ዲ​ሁም የሰው ነገሩ የል​ቡ​ና​ውን ፈቃድ ይገ​ል​ጥ​በ​ታል።

7 ሰውን ሳት​ረ​ዳው አታ​ድ​ን​ቀው፤ ሰውን ከሥ​ራው የተ​ነሣ ይፈ​ት​ኑ​ታ​ልና።

8 ጽድ​ቅን ብት​ከ​ተ​ላት ታገ​ኛ​ታ​ለህ፥ እንደ ከበረ ግም​ጃም ትለ​ብ​ሳ​ታ​ለህ።

9 ወፍ ከዘ​መዱ ጋር ይኖ​ራል፤ ጽድ​ቅም በሚ​ሠ​ሯት ሰዎች ዘንድ ትኖ​ራ​ለች።

10 አን​በሳ የሚ​በ​ላ​ውን ያድ​ናል፤ እን​ዲ​ሁም ኀጢ​አት የሚ​ሠ​ሯ​ትን ሰዎች ታድ​ና​ቸ​ዋ​ለች።

11 ጻድቅ ሰው ሁል​ጊዜ ጥበ​ብን ያስ​ተ​ም​ራል፤ የሰ​ነፍ ሰው ግን ዕው​ቀቱ እያ​ደረ እንደ ጨረቃ ይጐ​ድ​ላል።

12 በሰ​ነ​ፎች ዘንድ ጊዜ​ውን ተጠ​በቅ፤ በብ​ል​ሆች ሰዎች ዘንድ ግን ሁል​ጊዜ ተረዳ።

13 የሰ​ነ​ፎች ነገር ያበ​ሳ​ጫል፤ ሣቃ​ቸ​ውም የኀ​ጢ​አት ደስታ ነው።

14 ብዙ መሐ​ላን የሚ​ምል ሰው ነገር ፀጕ​ርን ያቆ​ማል፤ የት​ዕ​ቢ​ተኛ ሰው ክር​ክ​ርም ዦሮ ያደ​ነ​ቍ​ራል።

15 የት​ዕ​ቢ​ተ​ኞች ጠብ ደም ያፋ​ስ​ሳል፤ ክር​ክ​ራ​ቸ​ውም ለሚ​ሰ​ማ​ቸው ሰው ድካም ነው።


የባ​ል​ን​ጀ​ራን ምሥ​ጢር ማው​ጣት እን​ደ​ማ​ይ​ገባ

16 የባ​ል​ን​ጀ​ራ​ውን ምሥ​ጢር የሚ​ያ​ወጣ ሰው መታ​መ​ኑን ያጠ​ፋል፤ ከዚ​ህም በኋላ እንደ ልቡ የሚ​ሆን ወዳ​ጅን አያ​ገ​ኝም።

17 ወዳ​ጅ​ህን ጠብቅ፤ ከእ​ር​ሱም ጋራ ተማ​መን፤ ምሥ​ጢ​ሩን ብታ​ወ​ጣ​በት ግን በኋ​ላው አት​ከ​ተ​ለ​ውም።

18 ሰው ጠላ​ቱን እን​ደ​ሚ​ያ​ጠፋ፥ አን​ተም የወ​ዳ​ጅ​ህን ወን​ድ​ም​ነት ታጠ​ፋ​ለህ።

19 ወፍ ከእ​ጅህ እን​ደ​ም​ታ​መ​ልጥ፥ እን​ዲሁ ወዳ​ጅህ ከአ​ንተ ያመ​ል​ጣል።

20 ምዳቋ ከወ​ጥ​መድ እን​ደ​ም​ታ​መ​ልጥ፥ ከአ​ንተ አም​ልጦ ርቋ​ልና ከዚህ በኋላ አት​ከ​ተ​ለ​ውም።

21 ቍስል ቢሆን ባዳ​ኑት ነበር፤ የተ​ሰ​ደ​በ​ንም ሰው ባስ​ካ​ሱት ነበር፤ የባ​ል​ን​ጀ​ራ​ውን ምሥ​ጢር የሚ​ያ​ወ​ጣ​ውን ሰው ግን ተስፋ ይቈ​ር​ጡ​በ​ታል።


ስለ ግብ​ዝ​ነት

22 ክፋ​ቱን ማስ​ተው የሚ​ችል የለ​ምና፤ በዐ​ይኑ የሚ​ጠ​ቅስ ሰው ልቡ​ናው ያማረ አይ​ሆ​ንም።

23 ለዐ​ይ​ንህ ግን ከን​ፈ​ሩን ይመ​ጥ​ጥ​ል​ሃል፤ በተ​ና​ገ​ር​ኸ​ውም ሁሉ ያመ​ሰ​ግ​ን​ሃል፤ ኋላ ግን በቃሉ ይወ​ነ​ጅ​ል​ሃል፤ በተ​ና​ገ​ር​ኸው ቃል​ህም ያጠ​ም​ድ​ሃል።

24 የጠ​ላ​ኋ​ቸው ብዙ​ዎች ናቸው፤ ነገር ግን እንደ እርሱ አይ​ደ​ሉም፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም እር​ሱን ይጠ​ላል።

25 ድን​ጋ​ይን ወደ ላይ የሚ​ወ​ረ​ውር ሰው በራሱ ላይ ትወ​ር​ዳ​ለች፤ የበ​ደል ግር​ፋ​ትም ቍስሉ ይታ​ወ​ቃል።

26 ለባ​ል​ን​ጀ​ራው ጕድ​ጓድ የቈ​ፈረ ሰው፥ እርሱ በው​ስጡ ይወ​ድ​ቃል፤ ወጥ​መ​ድም ያዘ​ጋጀ ሰው ራሱ ይያ​ዝ​በ​ታል።

27 ሰው ኀጢ​አ​ትን ቢሠራ በእ​ርሱ ላይ ትመ​ለ​ሳ​ለች፤ ከየ​ትም እን​ደ​ም​ት​መጣ አያ​ው​ቅም።

28 የት​ዕ​ቢ​ተ​ኞች ስድ​ባ​ቸ​ውና ሣቃ​ቸው እንደ አን​በሳ ያድ​ኑ​አ​ቸ​ዋል፤ ይበ​ቀ​ሉ​አ​ቸ​ዋ​ልም።

29 በጻ​ድቅ ሰው መው​ደቅ ደስ የሚ​ላ​ቸው ሰዎች በወ​ጥ​መድ ይያ​ዛሉ፤ የሚ​ሞ​ቱ​በ​ትም ጊዜ ሳይ​ደ​ርስ መቅ​ሠ​ፍት ያጠ​ፋ​ቸ​ዋል።

30 ቍጣና መዓ​ትም የሚ​ያ​ስ​ጸ​ይፉ ናቸው፤ በኀ​ጢ​አ​ተኛ ሰውም ዘንድ ጸን​ተው ይኖ​ራሉ።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች