Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ

- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽሐፈ ሲራክ 25 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 በእ​ነ​ዚህ በሦ​ስቱ ነገ​ሮች ያማ​ርሁ ሆንሁ፤ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርና በሰው ፊትም ያማ​ርሁ ሆኜ ቆምሁ፥ እነ​ዚ​ህም በአ​ንድ ልብ የሚ​ተ​ባ​በሩ ወን​ድ​ማ​ማ​ቾች፥ የባ​ል​ን​ጀ​ሮች ፍቅር፥ የባ​ልና ሚስ​ትም ስም​ም​ነት ናቸው።

2 ሦስት ዐይ​ነት ሰዎ​ችን ሰው​ነቴ ፈጽማ ጠላ​ቻ​ቸው፤ ኑሯ​ቸ​ውም እጅግ አበ​ሳ​ጨኝ፤ እነ​ዚ​ህም ትዕ​ቢ​ተኛ ድሃ፥ ንፉግ ባለ​ጸ​ጋና አእ​ምሮ የሌ​ለው ሴሰኛ ሽማ​ግሌ ናቸው።

3 ከሕ​ፃ​ን​ነ​ትህ ጀም​ረህ ያል​ተ​መ​ከ​ርህ፥ በእ​ር​ጅ​ናህ ጊዜ እን​ዴት ብልህ ትሆ​ና​ለህ?

4 ሺበት ፍርድ ሊሰጥ ይገ​ባ​ዋል፤ ሽማ​ግ​ሎ​ችም መም​ከር ይገ​ባ​ቸ​ዋል።

5 ለሽ​ማ​ግ​ሎ​ችም ጥበብ ይገ​ባ​ቸ​ዋል፤ ለታ​ላ​ላቅ ሰዎ​ችም ጥበ​ብን መማር ይገ​ባ​ቸ​ዋል።

6 የት​ም​ህ​ርት ብዛት የሽ​ማ​ግ​ሎች ዘው​ዳ​ቸው ነው፤ መመ​ኪ​ያ​ቸ​ውም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን መፍ​ራት ነው።

7 በልቤ ያደ​ነ​ቅ​ኋ​ቸው ዘጠኝ ናቸው፤ ዐሥ​ረ​ኛ​ውን ግን በቃሌ እና​ገ​ራ​ለሁ፤ እነ​ር​ሱም በል​ጆቹ ደስ የሚ​ለው ሰው፥ በሕ​ይ​ወ​ቱም ሳለ የጠ​ላ​ቱን ውድ​ቀት የሚ​ያይ ሰው ናቸው።

8 ልባም ሴትን ያገባ ብፁዕ ነው፤ በአ​ን​ደ​በ​ቱም ያል​ሳተ ሰው ብፁዕ ነው፤ ከእ​ርሱ ላነሰ ሰው ያላ​ደረ ብፁዕ ነው፤

9 ዕው​ቀ​ትና ጥበ​ብን ያገ​ኛት ሰው፥ የሚ​ታ​ዘ​ዝ​ለ​ት​ንም ያገኘ ሰው ብፁዕ ነው።

10 ጥበ​ብን ያገኘ ሰው እን​ዴት ታላቅ ነው! ነገር ግን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የሚ​ፈራ ይህን ይበ​ል​ጠ​ዋል።

11 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን መፍ​ራት ከሁሉ ትበ​ል​ጣ​ለች።

12 እር​ሷ​ንም የጠ​በቀ ሰውን የሚ​መ​ስ​ለው የለም።

13 ከቍ​ስል ሁሉ ይልቅ የልብ ቍስል ይከ​ፋል፤ ከክ​ፋ​ትም ሁሉ የሴት ክፋት ትከ​ፋ​ለች።

14 በሁ​ሉም ብት​ወ​ድቅ በጠ​ላ​ትህ እጅ አት​ው​ደቅ፤ ሁሉ ቢበ​ቀ​ልህ ጠላ​ትህ አይ​በ​ቀ​ልህ።

15 ከእ​ባብ ራስ የሚ​ከፋ ራስ የለም፤ ከጠ​ላ​ትም ቂም የሚ​ከፋ ቂም የለም።


የክፉ ሴት ተግ​ባር

16 ከክፉ ሴት ጋራ ከም​ት​ኖር፥ ከአ​ን​በ​ሶ​ችና ከም​ድር አው​ሬ​ዎች ጋር መኖር ይሻ​ላል።

17 ክፋ​ትዋ መል​ኳን ይለ​ው​ጠ​ዋል፤ ፊት​ዋ​ንም እንደ ድብ መልክ ያጠ​ቍ​ረ​ዋል።

18 ባሏ​ንም በባ​ል​ን​ጀ​ሮቹ መካ​ከል ይን​ቁ​ታል፤ መራራ ኀዘ​ን​ንም ያሳ​ዝ​ኑ​ታል፤ አስ​ጨ​ን​ቀ​ውም ይይ​ዙ​ታል።

19 ክፋት ሁሉ ከሴት ክፋት ታን​ሳ​ለች፤ እር​ስ​ዋም ወደ ኀጢ​አት ዕድል ታደ​ር​ሳ​ለች።

20 የአ​ሸዋ ዐቀ​በት የሽ​ማ​ግ​ሌ​ዎ​ችን እግ​ራ​ቸ​ውን እን​ደ​ሚ​ያ​ደ​ክም፥ እን​ዲሁ ቀባ​ጣሪ ሴት የዋህ ባልን ታደ​ክ​መ​ዋ​ለች።

21 የሴት መልኳ አያ​ስ​ትህ፤ ሀብ​ቷም አያ​ስ​ጐ​ም​ጅህ። መቅ​ሠ​ፍ​ትና ጥፋት ጽኑ ውር​ደ​ትም ናትና፤

22 ሴት ባሏን ብት​መ​ግ​በው፥ ቍጣን፥ አለ​ማ​ክ​በ​ር​ንና ብዙ ዘለ​ፋን የተ​ሞ​ላች ትሆ​ና​ለች።

23 ለልብ ቍስል ናት፥ ለፊ​ትም ጥቁ​ረት ናት፥ ለነ​ፍ​ስም ኀዘን ናት፤ እን​ዲሁ ባሏን የማ​ታ​ከ​ብር ሴት እንደ ሽባ እጅና ልምሾ እንደ ሆነ እግር ናት።

24 በመ​ጀ​መ​ሪ​ያም ኀጢ​አት ከሴት ተገ​ኘች፤ በእ​ር​ስ​ዋም ምክ​ን​ያት ሁላ​ችን እን​ሞ​ታ​ለን።

25 ለውኃ መፍ​ሰሻ አታ​ብ​ጅ​ለት ለሴ​ትም የል​ብ​ህን ምሥ​ጢር አታ​ው​ጣ​ላት።

26 እንደ ጠባ​ይህ ካል​ሆ​ነች ፍታት፤ ከሰ​ው​ነ​ት​ህም ለያት።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች