Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ

- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽሐፈ ሲራክ 24 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


የጥ​በብ ክብር

1 ጥበብ ራስ​ዋን ታመ​ሰ​ግ​ና​ለች፤ በአ​ሕ​ዛ​ብም መካ​ከል ትመ​ካ​ለች።

2 በል​ዑ​ልም ጉባኤ ትና​ገ​ራ​ለች፤ በኀ​ይ​ሉም ፊት ትመ​ካ​ለች።

3 እን​ዲ​ህም አለች፦ እኔ ከል​ዑል አፍ ወጣሁ፤ ምድ​ር​ንም እንደ ጉም ሸፈ​ን​ኋት።

4 እኔ በሰ​ማይ ኖርሁ፤ ዙፋ​ኔ​ንም በደ​መና ዐምድ ላይ ዘረ​ጋሁ።

5 ብቻ​ዬ​ንም በሰ​ማይ ዳርቻ ዞርሁ፤ በው​ቅ​ያ​ኖስ መካ​ከ​ልም ተመ​ላ​ለ​ስሁ፤

6 በባ​ሕ​ርም ማዕ​በል ላይ በየ​ብ​ስም መካ​ከል ሁሉ፥ በሕ​ዝ​ቡና በአ​ሕ​ዛቡ ሁሉ ጥሪ​ትን አደ​ረ​ግሁ።

7 ከዚ​ህም ሁሉ በኋላ ዕረ​ፍ​ትን ፈለ​ግሁ፤ እን​ግ​ዲህ በማን ርስት አድ​ራ​ለሁ?

8 ከዚ​ህም በኋላ ሁሉን የፈ​ጠረ አዘ​ዘኝ፤ ፈጣ​ሪም ማደ​ሪ​ያ​ዬን አዘ​ጋ​ጀ​ልኝ፤ እን​ዲ​ህም አለኝ፦ “በያ​ዕ​ቆብ እደሪ፤ ርስ​ት​ሽም በእ​ስ​ራ​ኤል ይሁን።”

9 ዓለም ሳይ​ፈ​ጠር ወለ​ደኝ፥ ለዘ​ለ​ዓ​ለ​ሙም ከእ​ርሱ አል​ለ​ይም።

10 በተ​ቀ​ደሰ ማደ​ሪ​ያ​ውም በፊቱ አገ​ለ​ገ​ልሁ፤ በጽ​ዮ​ንም አደ​ርሁ።

11 እን​ዲ​ሁም በተ​ወ​ደ​ደ​ችው ከተማ ዐረ​ፍሁ፤ ግዛ​ቴም ባስ​ገ​ዛኝ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ነበር።

12 በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ርስት ዕድል ፋንታ፥ በከ​በረ ሕዝብ መካ​ከል ሥር ሰደ​ድሁ።

13 በሊ​ባ​ኖስ እን​ዳለ ዝግባ ከፍ ከፍ አልሁ፤ በኤ​ር​ሞን ተራራ እን​ዳለ ዋን​ዛም ገነ​ንሁ።

14 በውኃ ዳር እን​ዳለ ዘን​ባ​ባም ረዘ​ምሁ፤ በኢ​ያ​ሪኮ እን​ዳለ ጽጌ​ረዳ፥ በም​ድረ በዳ እን​ዳ​ለች እን​ዳ​ማ​ረች የዘ​ይት እን​ጨ​ትም መዓ​ዛዬ የተ​ወ​ደደ ሆነ፤ እንደ ዋርካ ዛፍም ገነ​ንሁ።

15 መዓ​ዛ​ዬም እንደ ቀና​ን​ሞ​ስና እንደ ደር​ሶኒ ሽቱ የተ​ወ​ደደ ሆነ፤ መዓ​ዛ​ዬም እን​ዳ​ማረ የሽቱ መዓዛ ሆነ፤ እንደ ልባ​ን​ጃና እንደ ጥርኝ፥ ሰጡ​ቃጤ እን​ደ​ሚ​ባል ሽቱም፥ በደ​ብ​ተራ ኦሪት እን​ዳለ እንደ ነጭ ዕጣን መዓ​ዛም የተ​ወ​ደደ ሆነ።

16 ቅር​ን​ጫ​ፎች እንደ ቡጥም ረዘሙ፤ ቅር​ን​ጫ​ፎ​ችም የክ​ብ​ርና የጌ​ት​ነት ቅር​ን​ጫ​ፎች ናቸው።

17 እኔስ እንደ ተወ​ደደ የወ​ይን ሐረግ መወ​ደ​ድን አስ​ገ​ኘሁ።

18 አበ​ባ​ዬም የክ​ብ​ርና የባ​ለ​ጸ​ግ​ነት ፍሬ ነው።

19 የም​ት​ወ​ዱኝ ሰዎች ሁሉ ወደ እኔ ኑ፤ ከፍ​ሬ​ዬም ትጠ​ግ​ባ​ላ​ችሁ።

20 ስም አጠ​ራሬ ከማር፥ ርስ​ት​ነ​ቴም ከሸ​ን​ኮር ይልቅ ይጣ​ፍ​ጣ​ልና።

21 የሚ​መ​ገ​ቡ​ኝም አይ​ጠ​ግ​ቡ​ኝም፤ የሚ​ጠ​ጡ​ኝም አይ​ሰ​ለ​ቹ​ኝም።

22 የሚ​ሰ​ማ​ኝም አያ​ፍ​ርም፤ ለእኔ የሚ​ገዙ ሰዎች አይ​ስ​ቱም።

23 ይህ ሁሉ ነገር የል​ዑል የሕጉ መጽ​ሐፍ ነው፤ ስለ ያዕ​ቆ​ብም ወገ​ኖች ርስት ሙሴ ያዘ​ዘ​በት ሕግ ነው።

24 በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የሚ​ጸና አይ​ደ​ክ​ምም፤ እርሱ ያጸ​ና​ችሁ ዘንድ ተከ​ተ​ሉት፤ ሁሉን የሚ​ችል ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ብቻ ነው፤ ከእ​ር​ሱም በቀር ሌላ አዳኝ የለም።

25 ጥበ​ብን እንደ ኤፌ​ሶን ፈሳሽ፥ በሚ​ያ​ዝ​ያም ወራት እን​ደ​ሚ​መላ እንደ ጤግ​ሮስ ፈሳሽ የሚ​መ​ላት እርሱ ነው።

26 ምክ​ር​ንም እንደ ኤፍ​ራ​ጥስ ፈሳሽ፥ ባዝ​መ​ራም ወራት እንደ ዮር​ዳ​ኖስ ፈሳሽ የሚ​መ​ላት እርሱ ነው።

27 ጥበ​ብን እንደ ብር​ሃን፥ በወ​ይን አዝ​መራ ወራ​ትም እንደ አባይ ፈሳሽ የሚ​ገ​ል​ጣት እርሱ ነው።

28 የመ​ጀ​መ​ሪ​ያው አላ​ወ​ቃ​ትም፤ የመ​ጨ​ረ​ሻ​ውም ፍለ​ጋ​ዋን አላ​ገ​ኘም።

29 ምሥ​ጢሯ ከባ​ሕር ውኃ ይልቅ ይበ​ዛል፤ ምክ​ሯም ከባ​ሕሩ ጥል​ቀት ይልቅ ይጠ​ል​ቃል።

30 ከወ​ንዝ እን​ደ​ሚ​ፈ​ስስ ውኃ ሆንሁ፤ እንደ መስኖ ውኃም ወደ ተክል ቦታ ገባሁ፤

31 እን​ዲ​ህም አልሁ፥ “የተ​ክል ቦታ​ዬን ላጠ​ጣት፤ የጎ​መን ቦታ​ዬን ላጠ​ጣት፤” ፈፋዬ እንደ ወንዝ ሆነ​ልኝ፤ ወን​ዜም እንደ ባሕር ሆነ​ልኝ።

32 ዳግ​መ​ኛም ጥበ​ብን እንደ ጥዋት አበ​ራ​ታ​ለሁ፤ እስከ ሩቅም ድረስ ብር​ሃ​ን​ዋን አሳ​ያ​ለሁ።

33 ትም​ህ​ር​ትን እንደ ትን​ቢት አፈ​ስ​ሳ​ታ​ለሁ፤ ለዘ​ለ​ዓ​ለ​ምም ለልጅ ልጅ አጸ​ና​ታ​ለሁ።

34 እነሆ፥ የደ​ከ​ምሁ ለሚ​ፈ​ል​ጉኝ ሰዎች ሁሉ ነው እንጂ፥ ለእኔ ብቻ እን​ዳ​ይ​ደለ እዩ።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች