Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ

- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽሐፈ ሲራክ 23 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ከኀ​ጢ​አት ስለ መራቅ ጸሎት

1 አቤቱ፥ አባቴ፥ የሕ​ይ​ወ​ቴም ፈጣሪ፥ በእ​ነ​ርሱ ምክር አት​ጣ​ለኝ፥ በእ​ነ​ር​ሱም እን​ዳ​ል​ጠፋ አት​ለ​የኝ፤

2 ልቡ​ና​ዬን ማን በመ​ከ​ረ​ልኝ? ድን​ቍ​ር​ና​ዬም ይተ​ወኝ ዘንድ፥ በተ​ና​ገ​ሩ​ብ​ኝም ነገር ድል እን​ዳ​ይ​ነ​ሱኝ፥ ለል​ቡ​ናዬ ጥበ​ብን ማን ባስ​ተ​ማ​ራት?

3 በደሌ እን​ዳ​ይ​በ​ዛ​ብኝ፥ ኀጢ​አ​ቴም እን​ዳ​ይ​በ​ረ​ክ​ት​ብኝ፥ በጠ​ላ​ቶ​ችም ፊት እን​ዳ​ል​ወ​ድቅ፥ ጠላ​ቶ​ችም በእኔ ጥፋት ደስ እን​ዳ​ይ​ላ​ቸው፥

4 ጌታዬ፥ አባቴ፥ የሕ​ይ​ወቴ ፈጣሪ ሆይ፥ ዐይ​ኔን የሚ​ያ​ስ​ታ​ትን ነገር አታ​ም​ጣ​ብኝ።

5 መጐ​ም​ጀ​ት​ንም ከእኔ አር​ቅ​ልኝ።

6 ጥጋብ አይ​ም​ጣ​ብኝ፤ ቍን​ጣ​ንም አያ​ቀ​ና​ጣኝ፤ ለክፉ ሰውም አሳ​ል​ፈህ አት​ስ​ጠኝ።


አን​ደ​በ​ትን ስለ መግ​ራት

7 ልጆች ሆይ፥ የአ​ን​ደ​በ​ቴን ምክር ስሙኝ፤ ቃሌን የጠ​በቀ አይ​ሰ​ነ​ካ​ከ​ልም፤ አን​ደ​በ​ቱ​ንም የጠ​በቀ አይ​ወ​ድ​ቅም።

8 ኀጢ​አ​ተኛ በስ​ን​ፍ​ናው ይያ​ዛል፤ ተሳ​ዳ​ቢና ትዕ​ቢ​ተ​ኛም በዚሁ ይሰ​ነ​ካ​ከ​ላሉ።

9 ልጄ ሆይ፥ ለአ​ፍህ መሐ​ላን አታ​ስ​ለ​ም​ደው፤ በማ​ል​ህም ጊዜ የቅ​ዱ​ሱን ስም በሐ​ሰት አት​ጥራ።

10 ሁል​ጊዜ እየ​ተ​መ​ረ​መረ የሚ​ገ​ረፍ ባሪያ ቍስሉ እን​ደ​ማ​ይ​ደ​ርቅ፥ እን​ደ​ዚሁ ሲምል ሁል​ጊዜ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ስም በሐ​ሰት የሚ​ጠራ ሰው ከኀ​ጢ​አት አይ​ነ​ጻም።

11 መሐ​ላን የሚ​ያ​በዛ ሰው ኀጢ​አቱ ብዙ ነው፥ ከቤ​ቱም መቅ​ሠ​ፍት አይ​ር​ቅም፤ ቢያ​ረ​ጅም ኀጢ​አቱ አይ​ተ​ወ​ውም፤ ቸል ቢልም ኀጢ​አቱ እጥፍ ይሆ​ን​በ​ታል፤ ፍዳው በቤቱ ሞል​ት​ዋ​ልና ስለ ማለ እው​ነ​ተኛ አይ​ባ​ልም።

12 ሞትን የም​ታ​መ​ጣው ቃል አለች፤ በያ​ዕ​ቆ​ብም ርስት አት​ኖ​ርም፤ ይህ ሁሉ በጻ​ድ​ቃን ዘንድ የለም፤ በኀ​ጢ​አ​ትም አይ​ሰ​ነ​ካ​ከ​ሉም።

13 በው​ስጡ ብዙ ኀጢ​አት አለና፥ ከአ​ን​ደ​በ​ትህ የመ​ዘ​ባ​በት ነገር አይ​ውጣ።

14 አባ​ት​ህ​ንና እና​ት​ህን ዐስ​ባ​ቸው፥ መኳ​ን​ን​ቶ​ች​ህ​ንም አገ​ል​ግል፤ በፊ​ታ​ቸ​ውም አት​ሳት፤ ባል​ተ​ወ​ለ​ድሁ እን​ዳ​ትል፥ የተ​ወ​ለ​ድ​ህ​በ​ት​ንም ቀን እን​ዳ​ት​ረ​ግም በስ​ን​ፍ​ናህ እን​ዳ​ት​ጠላ ሁን።

15 በሰው ላይ መሳ​ለ​ቅን የለ​መደ ሰው፥ መላ ሕይ​ወ​ቱን ብልህ አይ​ሆ​ንም።


ስለ ዝሙት ኀጢ​አት

16 ኀጢ​አ​ትን የሚ​ያ​መ​ጧት ሁለት ናቸው፤ ሦስ​ተ​ኛው ግን ሞትን ያመ​ጣል፤ ቍጡ ሰው​ነት እን​ደ​ሚ​ቃ​ጠል እሳት ናት፤ እስ​ክ​ታ​ሰ​ጥ​መ​ውም ድረስ አት​በ​ር​ድም፤ በሰ​ው​ነ​ቱም የሚ​ሰ​ስን ሰው እሳ​ትን እስ​ኪ​ያ​ቀ​ጣ​ጥ​ላት ድረስ አይ​ተ​ውም።

17 ለሴ​ሰኛ ሰው እህሉ ሁሉ ይጣ​ፍ​ጠ​ዋል፤ እስ​ኪ​ሞ​ትም ድረስ አያ​ር​ፍም።

18 ሚስ​ቱን ትቶ የሚ​ሄድ ሰው፥ በልቡ “ጊዜው ጨለማ ነው፤ የሚ​ያ​የኝ የለም፤ አጥር ይጋ​ር​ደ​ኛል፤ ከዚህ በኋላ ምን እፈ​ራ​ለሁ? የሚ​ያ​ው​ቀ​ኝም የለም፤ ልዑ​ልም ኀጢ​አ​ቴን ይዘ​ነ​ጋ​ል​ኛል፤ አያ​ስ​ብ​ብ​ኝ​ምም” ይላል።

19 ነገር ግን እን​ዳ​ያ​የው የሰው ዐይ​ንን ይፈ​ራል፤ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ዐይን ከፀ​ሐይ መቶ ሺህ ጊዜ እን​ዲ​በራ፥ የሰ​ው​ንም ሥራ ሁሉ እን​ደ​ሚ​ያይ፥ ተሰ​ውሮ የሚ​ሠ​ራ​ንም ሥራ ሁሉ እን​ደ​ሚ​ያ​ውቅ አያ​ው​ቅም።

20 ሁሉም ከመ​ፈ​ጠሩ በፊት በእ​ርሱ ዘንድ የታ​ወቀ ነው፤ ከጨ​ረ​ሰም በኋላ እን​ዲህ ያደ​ር​ገ​ዋል።

21 በከ​ተ​ማም መካ​ከል ይበ​ቀ​ለ​ዋል፤ ባል​ጠ​ረ​ጠ​ረ​በ​ትም ቦታ ያጠ​ፋ​ዋል።

22 ባሏን ትታ የም​ት​ሄድ ሴት እን​ዲሁ ናት፤ ከሌላ ወንድ ልጅን ትወ​ል​ዳ​ለች።

23 በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አን​ዲት ክህ​ደት አደ​ረ​ገች፤ ሁለ​ተ​ኛም ባሏን ከዳ​ችው፥ ሦስ​ተ​ኛም በሴ​ሰ​ኝ​ነ​ትዋ ሰረ​ቀች፤ ከሌላ ወን​ድም ልጅን ወለ​ደች።

24 እን​ዲህ ያለ​ችው ሴት ቷረ​ዳ​ለች፤ በል​ጆ​ች​ዋም ትገ​ረ​ፋ​ለች።

25 ዘሮ​ችዋ ይጠ​ፋሉ፤ ቅር​ን​ጫ​ፎ​ች​ዋም አያ​ፈ​ሩም።

26 ስም አጠ​ራ​ሯም የተ​ረ​ገመ ይሆ​ናል፤ ለቤ​ቷም መር​ገ​ምን ታወ​ር​ሳ​ለች፤ መር​ገ​ም​ዋና ውር​ደቷ ለዘ​ለ​ዓ​ለሙ አይ​ጠ​ፋም።

27 ያያት ሁሉ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ከመ​ፍ​ራት የሚ​በ​ልጥ፥ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ሕግ ከመ​ጠ​በቅ የሚ​ጣ​ፍጥ እን​ደ​ሌለ ያው​ቃል።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች