Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ

- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽሐፈ ሲራክ 22 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ሰነ​ፍና ስን​ፍና

1 ሰነፍ ሰው በተ​ቀ​መ​ጠ​በት ቦታ እንደ ዋሻ ድን​ጋይ ነው፤ በጽኑ ስን​ፍ​ናው ሁሉን ያቦ​ዝ​ናል።

2 ሰነፍ ሰው በተ​ኛ​በት ቦታ እንደ ተጣለ ፈርስ ነው። የነ​ካ​ውም ሰው ሁሉ እጁን ያራ​ግ​ፋል።

3 ያል​ተ​ቀጣ ልጅ ለአ​ባቱ ኀፍ​ረት ነው፤ ያል​ተ​ቀ​ጣች ሴት ልጅም የጐ​ሰ​ቈ​ለች ትሆ​ና​ለች።

4 ብልህ ሴት ልጅ ባል​ዋን ትወ​ር​ሳ​ለች፤ የም​ታ​ሳ​ፍር ሴት ልጅ ግን ለአ​ባቷ ኀዘን ናት።

5 አባ​ት​ዋ​ንም ታሳ​ፍ​ራ​ለች፤ ባሏ​ንም ታሳ​ፍ​ራ​ለች፤ ደፋ​ርም ናት፤ በሁ​ለ​ቱም ዘንድ እጥፍ ቷረ​ዳ​ለች።


ጥበ​ብና ሞኝ​ነት

6 ባገ​ኘ​በት ቦታ ነገ​ሩን የሚ​ና​ገር ሰው፥ በል​ቅሶ ቤት መሰ​ንቆ እን​ደ​ሚ​መታ ሰው ነው፤ ግር​ፋ​ትና ተግ​ሣጽ ሁል​ጊዜ ብልህ ያደ​ር​ጋል።

7 ሰነፍ ሰውን የሚ​ያ​ስ​ተ​ምር ሰው፥ የተ​ሰ​በረ ገልን እን​ደ​ሚ​ጠ​ግን ሰው ነው፤ የተኛ ሰው​ንም ከጽኑ እን​ቅ​ልፍ እንደ መቀ​ስ​ቀስ ነው።

8 ለሰ​ነፍ ሰው የሚ​ነ​ግር በጽ​ኑዕ እን​ቅ​ልፍ ለተ​ያዘ ሰው እን​ደ​ሚ​ነ​ግር ነው፤ ነግ​ረ​ኸው ከጨ​ረ​ስህ በኋላ “ምን ተና​ገ​ርኽ?” ይል​ሃል።

9 ብር​ሃኑ አል​ፏ​ልና ለሞተ ሰው አል​ቅ​ስ​ለት፤ አእ​ም​ሮ​ውም ጠፍ​ት​ዋ​ልና ለሰ​ነፍ ሰው አል​ቅ​ስ​ለት።

10 ከሞተ በኋላ አይ​መ​ለ​ስ​ምና፥ ለሞተ ሰው ታለ​ቅ​ስ​ለት ዘንድ አገ​ባብ ነው። ከመ​ሞቱ መኖሩ ይከ​ፋ​በ​ታ​ልና ለሰ​ነፍ ሰው በሕ​ይ​ወት ሳለ አል​ቅ​ስ​ለት።

11 ሰዎች ስለ ሞተ ሰው ሰባት ቀን ያለ​ቅ​ሱ​ለ​ታል፤ ለሰ​ነ​ፍና ለኀ​ጢ​አ​ተኛ ግን በሕ​ይ​ወት ዘመኑ ሁሉ አል​ቅ​ስ​ለት።

12 ከሰ​ነፍ ሰው ጋራ ነገ​ርን አታ​ብዛ፤ አእ​ምሮ ከሌ​ለ​ውም ሰው ጋራ አት​ሂድ፤ ወደ መከራ እን​ዳ​ያ​ገ​ባህ፥ አን​ተም በእ​ርሱ ስን​ፍና እን​ዳ​ት​ነ​ቀፍ ተጠ​በቅ።

13 ከእ​ርሱ ራቅ፤ ሰው​ነ​ት​ህም ታር​ፋ​ለች፤ ይቀ​ል​ሃ​ልም፤ በእ​ር​ሱም ስን​ፍና አንተ የም​ት​ጐ​ዳው የለም።

14 ከአ​ረር የሚ​ከ​ብድ ምን አለ? ሰነፍ ከመ​ባ​ልስ የሚ​ከፋ ምን አለ?

15 ከሰ​ነፍ ሰው ጋራ ከመ​ኖር፥ ጨውና አሸዋ፥ ብረ​ት​ንም ብት​ሸ​ከም ይሻ​ላል።

16 ማገሩ ያማረ፥ በግ​ንብ የታ​ሰረ ቤት በም​ድር መና​ወጥ ጊዜ እን​ደ​ማ​ይ​ፈ​ርስ፥ የብ​ልህ ሰው ምክ​ርም በጽ​ኑዕ ልቡና እን​ዲሁ ነው።

17 ቅጥ​ሩም ለዘ​ለ​ዓ​ለም አይ​ወ​ድ​ቅም፤ በዐ​ዋቂ ሰው ምክር የጸና ልቡ​ናም በግ​ድ​ግዳ ላይ እን​ዳለ የአ​ሸዋ ምርግ ነው።

18 በነ​ፋስ ፊት ያለ ገለ​ባም ነፋስ በነ​ፈሰ ጊዜ እን​ደ​ማ​ይ​ቆም፥ ያላ​ዋቂ ሰው ዐሳ​ብም ያስ​ፈ​ራው ሰው ቢኖር በማ​ይ​ቆም በፈሪ ሰው ልቡና ዘንድ እን​ዲሁ ነው።


ወዳ​ጅ​ነ​ትን ጠብቆ ማቈ​የት

19 ዐይ​ኑን የሚ​ጠ​ነ​ቍል ሰው እን​ባ​ውን ያወ​ር​ዳል፤ ልቡ​ና​ው​ንም የሚ​ነካ ሰው ጥበ​ብን ያሳ​ያል።

20 በወ​ፎች ድን​ጋይ የወ​ረ​ወ​ረ​ባ​ቸው ሰው ያባ​ር​ራ​ቸ​ዋል፤ በወ​ዳ​ጁም የሚ​ዘ​ብት ሰው ወዳ​ጅ​ነ​ትን ያጠ​ፋል።

21 በወ​ዳ​ጅህ ላይ ሰይ​ፍን ብት​መዝ፥ ተመ​ልሶ ወዳ​ጅህ ይሆን ይሆ​ና​ልና ተስፋ አት​ቍ​ረጥ።

22 ነገር ግን ብት​ላ​ገ​ድ​በት፥ አፍ​ህ​ንም በእ​ርሱ ላይ ከፍና ዝቅ አድ​ር​ገህ ብት​ና​ገር፥ ብት​ሰ​ድ​በ​ውም፥ ምክ​ሩ​ንም ብታ​ወ​ጣ​በት፥ ብት​ከ​ዳ​ውና፥ ብታ​ሳ​ዝ​ነው በዚህ ነገር ወዳጅ ሁሉ ይሸ​ሻል።

23 አን​ተም ድሃ ብት​ሆን በደ​ስ​ታው ጊዜ ከእ​ርሱ ጋር ደስ ይልህ ዘንድ፥ ከባ​ል​ን​ጀ​ራህ ጋር ታማ​ኝ​ነ​ት​ህን ጠብቅ። ቢቸ​ገ​ርም ርስ​ቱን ባገኘ ጊዜ ከእ​ርሱ ጋር ደስ ይልህ ዘንድ ከእ​ርሱ ጋር ታገሥ።

24 የእ​ሳ​ትም የጭሱ ትነት ይቀ​ድ​ማል፤ እን​ደ​ዚ​ሁም ደም ከማ​ፍ​ሰስ ጠብና ክር​ክር ይቀ​ድ​ማል።

25 ወዳ​ጄን መሰ​ወር አላ​ፍ​ርም፤ ከፊ​ቱም አል​ሰ​ወ​ርም።

26 ነገር ግን በእ​ርሱ ምክ​ን​ያት ክፋት ብታ​ገ​ኘኝ፥ የሰማ ሁሉ ከእ​ርሱ ራሱን ይጠ​ብቅ።

27 ለአ​ን​ደ​በቴ ጠባቂ ማን ባኖ​ረ​ልኝ? በእ​ነ​ርሱ እን​ዳ​ል​ወ​ድቅ፥ አን​ደ​በ​ቴም እን​ዳ​ት​ገ​ድ​ለኝ፥ በከ​ን​ፈ​ሮች የጥ​በ​ብን ቍልፍ ማን ባኖ​ረ​ልኝ!

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች