Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ

- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽሐፈ ሲራክ 21 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 ልጄ ሆይ፥ የበ​ደ​ል​ኸው በደል የሳ​ት​ኸ​ውም ነገር ቢኖር፥ እን​ዳ​ት​ደ​ግም ተጠ​ን​ቀቅ፥ ስለ ቀደ​መው ኀጢ​አ​ት​ህም ንስሓ ግባ።

2 ከክፉ አውሬ እን​ደ​ሚ​ሸሽ እን​ዲሁ ከኀ​ጢ​አት ሽሽ፥ ከአ​ገ​ኘ​ችህ ግን አት​ለ​ቅ​ህም፤ ጥርሷ እንደ አን​በሳ ጥርስ ነው፤ የሰ​ው​ንም ነፍስ ታጠ​ፋ​ለች።

3 ሁለት አፍ እን​ዳ​ለው የተ​ሳለ ሰይፍ ኀጢ​አት ሁሉ እን​ዲሁ ናት፤ ካቈ​ሰ​ለ​ችም ለቍ​ስሏ ፈውስ የለ​ውም።

4 መመ​ካ​ትና መኵ​ራት፥ ትዕ​ቢ​ትም ባለ​ጸ​ግ​ነ​ትን ያጠ​ፏ​ታል፤ እን​ደ​ዚ​ሁም የት​ዕ​ቢ​ተ​ኞ​ችን ቤት ያጠ​ፋሉ።

5 ድሃ በሚ​ለ​ም​ን​በት ጊዜ አፉን እስከ ዦሮው ይከ​ፍ​ታል፤ ጩኸ​ቱም ፈጥኖ ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይደ​ር​ሳል።

6 ምክ​ርን የሚ​ጠላ ሰው ኀጢ​አ​ተ​ኞ​ችን ይከ​ተ​ላ​ቸ​ዋል፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የሚ​ፈራ ሰው ግን በመ​ከ​ሩት ጊዜ ልቡ​ና​ውን ይመ​ል​ሳል።

7 ንግ​ግ​ርን የሚ​ችል ሰው ከሩቁ ይታ​ወ​ቃል፤ ለብ​ልህ ሰውም የተ​ሳ​ተው ኀጢ​አቱ ይታ​ወ​ቀ​ዋል።

8 በብ​ድር ገን​ዘብ ቤቱን የሚ​ሠራ ሰው፥ ሕን​ጻው እንደ ክረ​ምት ግንብ ነው።

9 የኀ​ጢ​አ​ተ​ኞ​ችም አን​ድ​ነ​ታ​ቸው እንደ ገለባ ክምር ነው፤ ፍጻ​ሜ​ያ​ቸ​ውም ለእ​ሳት ነበ​ል​ባል ይሆ​ናል።

10 የኀ​ጢ​አ​ተ​ኞች መን​ገድ ጐፃ​ጕፅ ነው፤ መው​ጫ​ዋም ገደል ነው።

11 ልቡ​ና​ውን ያጸና ሰው የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ሕግ ይጠ​ብ​ቃል። እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የመ​ፍ​ራ​ትም መጨ​ረ​ሻዋ ጥበብ ነው።

12 ያል​ተ​ማረ ሰው ጠቢብ አይ​ሆ​ንም፤ ተም​ሮም ውር​ደት የሚ​በ​ዛ​በት አለ።

13 የብ​ልህ ሰው ዐሳቡ እንደ ክረ​ምት ውኃ ብዙ ነው፤ ምክ​ሩም እንደ ሕይ​ወት ውኃ ይመ​ነ​ጫል፤

14 ያላ​ዋቂ ሰው ልብ እንደ ሰባራ ማድጋ ነው፤ የሰ​ማ​ውን ነገር ሁሉ መጠ​በቅ አይ​ች​ል​ምና።

15 አስ​ተ​ዋይ ሰው የጥ​በ​ብን ነገር በሰማ ጊዜ ያደ​ን​ቃ​ታል፤ ዳግ​መ​ኛም በእ​ር​ስዋ ላይ ይጨ​ም​ራል፤ አላ​ዋቂ ልቡና ግን ከሰማ በኋላ ይተ​ፋል፤ ወደ ኋላም ይመ​ል​ሰ​ዋል።

16 የአ​ላ​ዋቂ ሰው ነገሩ በራቀ ጎዳና እን​ዳለ እን​ደ​ሚ​ከ​ብድ ሸክም ነው፤ የብ​ልህ ሰው አን​ደ​በት መወ​ደድ ግን መል​ካም ነው።

17 የብ​ልህ ሰው ነገሩ በጉ​ባኤ ይሰ​ማል፤ ነገ​ሩም ወደ ልብ ይገ​ባል።

18 ጥበብ በአ​ላ​ዋ​ቂ​ዎች ሰዎች ዘንድ እንደ ፈረ​ሰች ቤት ናት። ያላ​ዋቂ ሰው ምክ​ርም የማ​ይ​ወ​ደድ ነገር ነው።

19 ያላ​ዋ​ቂ​ዎች ትም​ህ​ርት እንደ ታሰረ እግር ነው። ያላ​ዋ​ቂ​ዎ​ችም ልቡና ቀኝ እጁን እንደ ታሰረ ሰው ደካማ ነው።

20 አላ​ዋቂ ሰው በሳቀ ጊዜ ቃሉን ከፍ ያደ​ር​ጋል፤ ብልህ ሰው ግን በጭ​ንቅ ከን​ፈ​ሩን ፈገግ ያደ​ር​ጋል።

21 ጥበብ በአ​ስ​ተ​ዋይ ሰው ዘንድ እንደ ወርቅ ጌጥ ናት፥ በቀኝ እጅ እን​ዳለ አም​ባ​ርም ናት።

22 ያላ​ዋቂ ሰው እግር ፈጥና ወደ ቤት ትገ​ባ​ለች፤ በት​ም​ህ​ርት የተ​ፈ​ተነ ሰው ግን የሰ​ውን ፊት ያፍ​ራል።

23 አላ​ዋቂ ሰው በደ​ጃፍ ሆኖ የሰው ቤትን ይመ​ለ​ከ​ታል፤ ዐዋቂ ሰው ግን በውጭ ይቆ​ማል።

24 ለሰው በበር ተጠ​ግቶ ማድ​መጥ አላ​ዋ​ቂ​ነት ነው፤ በዐ​ዋቂ ሰው ዘንድ ግን ይህን ነገር ማድ​ረግ እጅግ አሳ​ፋሪ ነው።

25 የለ​ፍ​ላፊ ከን​ፈር የማ​ይ​መ​ለ​ከ​ተ​ውን ይና​ገ​ራል፤ የጠ​ቢ​ባን ቃል ግን በሚ​ዛን የተ​መ​ዘ​ነች ናት።

26 ያላ​ዋ​ቆች ልባ​ቸው ባፋ​ቸው ነው፤ የኣ​ዋ​ቂ​ዎች አፍ ግን በል​ባ​ቸው ነው።

27 ኀጢ​አ​ተኛ ሰው ሰይ​ጣ​ንን ቢረ​ግ​መው ራሱን መር​ገሙ ነው።

28 ሐሜ​ተኛ ሰው ሰው​ነ​ቱን ያረ​ክ​ሳል፤ ባደ​ረ​በ​ትም ቦታ ራሱን ያስ​ጠ​ላል።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች