Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ

- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽሐፈ ሲራክ 20 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 ለበጎ ነገር ሳይ​ሆን የሚ​ገ​ሥጽ ሰው አለ፤ ዐዋቂ ሆኖ ሳለም ዝም የሚል ሰው አለ።

2 ነገር ግን ከመ​ን​ቀፍ መገ​ሠጽ ይሻ​ላል።

3 ስሕ​ተ​ቱን የሚ​ያ​ምን ከጥ​ፋት ይድ​ናል።

4 ፍር​ድን ያደላ ዘንድ የሚ​ወድ ሰው፥ ቆንጆ ልጅን እን​ደ​ሚ​መኝ ጃን​ደ​ረባ ነው።

5 እያ​ወቀ ዝም የሚል ሰው አለ፥ ንግ​ግር በማ​ብ​ዛ​ትም ራሱን የሚ​ያ​ስ​ጠላ ሰው አለ።

6 የሚ​መ​ል​ሰ​ውን አያ​ው​ቅ​ምና ዝም የሚል ሰው አለ፤ ጊዜ​ው​ንም እስ​ኪ​ያ​ገኝ ድረስ ዝም የሚል ሰው አለ።

7 ብልህ ሰውም ጊዜ​ውን እስ​ኪ​ያ​ገኝ ድረስ ዝም ይላል፤ አላ​ዋ​ቂና ደፋር ሰው ግን እን​ዳ​ገኘ ይና​ገ​ራል።

8 ነገ​ርን የሚ​ያ​በዛ ሰውን ይቈ​ጡ​ታል፤ ራሱ​ንም የሚ​ያ​ኰራ ሰውን ይጠ​ሉ​ታል።

9 ችግሩ የሚ​ያ​ዋ​ር​ደው ሰው አለ፤ ገን​ዘ​ብም አግ​ኝቶ የማ​ይ​በ​ረ​ክ​ት​ለት ሰው አለ።

10 የማ​ይ​ጠ​ቅ​ም​ህን የሚ​ሰ​ጥህ ሰው አለ፤ ሰጥ​ቶም እጥፍ አድ​ርጎ የሚ​ቀ​በ​ልህ ሰው አለ።

11 እየ​ተ​ቸ​ገረ ራሱን የሚ​ያ​ኰራ አለ፤ ራሱን በማ​ዋ​ረ​ዱም የሚ​ከ​ብር አለ።

12 በጥ​ቂት ብዙ የሚ​ገዛ አለ፤ ሰባት እጥፍ ያደ​ር​ገ​ውም ዘንድ ይፈ​ል​ጋል።

13 ብልህ ሰው በቃሉ ራሱን ያስ​ወ​ድ​ዳል፤ የአ​ላ​ዋ​ቂ​ዎች ስጦ​ታም ተወ​ዳ​ጅ​ነት የላ​ትም።

14 አላ​ዋቂ ሰው ጥቅ​ምና ተወ​ዳ​ጅ​ነት የሌ​ለ​ውን ገን​ዘብ ይሰ​ጥ​ሃል፤ ጥቂት ቢሰ​ጥ​ህም ለልቡ ብዙ የሰ​ጠህ ይመ​ስ​ለ​ዋል።

15 ጥቂት ቢሰ​ጥህ ብዙ እንደ ሰጠህ ይላ​ገ​ድ​ብ​ሃል፤ በአ​ን​ተም ላይ ነገ​ሩን ያበ​ዛል፤ የሰ​ጠ​ህ​ንም ይና​ገ​ር​ብህ ዘንድ በአ​ደ​ባ​ባይ ይዞ​ራል፤ ዛሬ ቢሰ​ጥህ ነገ ይከ​ፈ​ል​ሃል፥ እን​ዲህ ያለው ሰው የሚ​ያ​ስ​ጠላ ነው።

16 አላ​ዋቂ ሰው ግን “ወዳጅ አል​ፈ​ል​ግም ምን ይጠ​ቅ​መ​ኛል? በጎ ነገር ያደ​ረ​ግ​ሁ​ለት እኔ ዋጋን አላ​ገ​ኝ​ምና፤ እህ​ሌ​ንም የሚ​መ​ገቡ ሰዎች በእኔ ክፉ ነገር ይና​ገ​ራሉ።

17 ሁሉም ሁል​ጊዜ ያሙ​ኛል፤ በእ​ኔም ይስ​ቃሉ” ይላል።


የማ​ይ​ገባ ንግ​ግር

18 በአ​ን​ደ​በ​ትህ አድ​ጦህ ከም​ት​ወ​ድቅ፥ በም​ድር ላይ አድ​ጦህ ብት​ወ​ድቅ ይሻ​ል​ሃል፤ እን​ዲሁ የክፉ ሰው አወ​ዳ​ደቅ ፈጥኖ ይመ​ጣል።

19 እን​ዳ​ገኘ የሚ​ና​ገር ሰው ራሱን ያስ​ነ​ው​ራል፤ ለቃ​ሉም መወ​ደድ የለ​ውም፤ በአ​ላ​ዋ​ቂ​ዎች አን​ደ​በ​ትም ነገር ይጠ​ላል።

20 በጊ​ዜው አይ​ና​ገ​ረ​ው​ምና፥ በአ​ላ​ዋቂ ሰው አን​ደ​በት ምሳሌ ይጠ​ላል።

21 በተ​ቸ​ገረ ጊዜ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ወደ መፍ​ራት የሚ​መ​ለስ ሰው አለ፤ ሰው​ነ​ቱም በመ​ል​ካም ታር​ፋ​ለች።

22 በማ​ፈ​ርም ሰው​ነ​ቱን የሚ​ያ​ጠፋ አለ፤ በአ​ላ​ዋ​ቂ​ነ​ቱም ሰው​ነ​ቱን ያጠ​ፋል።

23 በማ​ፈር ላይ​ሰ​ጠው ለወ​ዳጁ ተስፋ የሚ​ሰ​ጠው አለ። ስለ​ዚ​ህም ነገር በከ​ንቱ ጠላት ይሆ​ነ​ዋል።

24 የሐ​ሰ​ተኛ ሰው ውር​ደቱ ክፉ ነው፤ የአ​ላ​ዋ​ቂ​ዎች ነገ​ራ​ቸው የተ​ጠላ ነው።

25 ከሐ​ሰ​ተኛ ሌባ ይሻ​ላል፤ ነገር ግን የሁ​ለ​ቱም ፍጻ​ሜ​ያ​ቸው ሞትና ውር​ደት ነው።

26 ሐሰ​ተኛ ሰው ፈጽሞ ይዋ​ረ​ዳል፥ ያፍ​ራ​ልም።

27 በቃሉ ብልህ የሆነ ሰው ነገሩ ይሰ​ማል፤ ብልህ ሰው መኳ​ን​ን​ቱን ደስ ያሰ​ኛል።

28 ምድ​ርን የሚ​ያ​ር​ሳት የእ​ህ​ሉን ክምር ያበ​ዛል፤ መኳ​ን​ን​ቱ​ንም የሚ​ያ​ገ​ለ​ግል ራሱን ይጠ​ቅ​ማል።

29 እጅ መን​ሻና መማ​ለጃ የጠ​ቢ​ባ​ንን ዐይን ያሳ​ው​ራል፤ አፋ​ቸ​ውን ይዘ​ጋል፤ ቃላ​ቸ​ው​ንም ያስ​ለ​ው​ጣል።

30 የተ​ሰ​ወረ ጥበብ እንደ ተቀ​በረ ወርቅ ነው፤ እን​ግ​ዲህ የሁ​ለ​ቱስ ጥቅ​ማ​ቸው ምን​ድን ነው?

31 ጥበ​ቡን ከሚ​ሰ​ውር ብልህ ሰው፤ አለ​ማ​ወ​ቁን የሚ​ሰ​ውር አላ​ዋቂ ሰው ይሻ​ላል።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች