Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽሐፈ ሲራክ 2 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ታማኝ ስለ መሆን

1 ልጄ ሆይ፥ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ትገዛ ዘንድ ብት​ሄድ ሰው​ነ​ት​ህን ለመ​ከራ አዘ​ጋጅ።

2 ልብ​ህን አቅና፥ ታገሥ፥ አታ​ወ​ላ​ው​ልም፥ ብት​ጨ​ነ​ቅም አት​ጠ​ራ​ጠር።

3 ነገር ግን ተከ​ተ​ለው፥ በፍ​ጻ​ሜ​ህም ሕይ​ወ​ትህ ትበ​ለ​ጽግ ዘንድ አት​ተ​ወው።

4 የደ​ረ​ሰ​ብ​ህን ሁሉ ተቀ​በል፥ በች​ግ​ር​ህም ወራት ታገሥ።

5 ወር​ቅን በእ​ሳት ይፈ​ት​ኑ​ታ​ልና፥ ጻድ​ቅ​ንም ሰው በመ​ከራ ይፈ​ት​ኑ​ታ​ልና።

6 ነገር ግን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን እመ​ነው፤ እር​ሱም ይረ​ዳ​ሃል፤ መን​ገ​ድ​ህ​ንም አቅና፥ በእ​ር​ሱም እመን።

7 እና​ንተ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የም​ት​ፈ​ሩት ሆይ፥ ቸር​ነ​ቱን ደጅ ጥኗት፥ በመ​ከ​ራም እን​ዳ​ት​ወ​ድቁ ከእ​ርሱ አት​ራቁ።

8 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የም​ት​ፈ​ሩት ሆይ፥ ዋጋ​ች​ሁን እን​ዳ​ታጡ እመ​ኑት።

9 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የም​ት​ፈሩ ሆይ፥ የዘ​ለ​ዓ​ለም በጎ​ነ​ቱን ምሕ​ረ​ቱ​ንና ደስ​ታ​ውን ተስፋ አድ​ርጉ።

10 በዘ​መን የቀ​ደሙ ሰዎ​ችን ተመ​ል​ከቱ፤ ዕወ​ቁም፥ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አምኖ ያፈረ ማን​ነው? እር​ሱን በመ​ፍ​ራት የታ​ገ​ሠና የተ​ጣለ ማን​ነው? ጠር​ቶ​ትስ ቸል ያለው ማን​ነው?

11 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መሓሪ ይቅር ባይም ነውና፥ ኀጢ​አ​ትን ይቅር ይላል፥ በመ​ከራ ቀንም ያድ​ናል።

12 ለሚ​ጠ​ራ​ጠር ልቡና ወዮ​ለት! ለጠ​ማ​ሞች እጆ​ችም ወዮ​ላ​ቸው! ሥራው ሁለት ለሆነ፥ በሁ​ለ​ትም መን​ገድ ለሚ​ሄድ ኀጢ​አ​ተኛ ወዮ​ለት!

13 ለሚ​ጠ​ራ​ጠ​ርና ለማ​ያ​ም​ንም ልብ ወዮ​ለት! ስለ​ዚ​ህም አያ​መ​ል​ጥም።

14 ትዕ​ግ​ሥ​ታ​ቸ​ውን ላጡ ሰዎች ወዮ​ላ​ቸው! እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በተ​መ​ለ​ሰ​ባ​ቸው ጊዜ ምን ያደ​ርጉ ይሆን?

15 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የሚ​ፈሩ ቃሉን አይ​ረ​ሱም፥ የሚ​ወ​ዱ​ትም ትእ​ዛ​ዙ​ንና መን​ገ​ዱን ይጠ​ብ​ቃሉ።

16 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የሚ​ፈሩ ሰዎች ፈቃ​ዱን ይሻሉ፤ የሚ​ወ​ዱ​ትም በሕጉ ይረ​ካሉ፤

17 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የሚ​ፈሩ ልቡ​ና​ቸ​ውን ያዘ​ጋ​ጃሉ። በፊ​ቱም ሰው​ነ​ታ​ቸ​ውን ያዋ​ር​ዳሉ።

18 በሰው እጅ ከም​ን​ወ​ድቅ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እጅ እን​ው​ደቅ፥ እንደ ልዕ​ል​ናው የቸ​ር​ነቱ ብዛት እን​ዲሁ ነውና።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች