Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ

- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽሐፈ ሲራክ 19 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 ሰካ​ራም ሠራ​ተኛ አይ​በ​ለ​ጥ​ግም፥ ጥቂ​ቱን የሚ​ያ​ቃ​ልል ብዙ​ውን ያጠ​ፋል።

2 መጠ​ጥና ሴት ጠቢ​ባ​ንን ያስ​ት​ዋ​ቸ​ዋል፥ ጋለ​ሞ​ታን የሚ​ከ​ተ​ላት በደ​ለኛ ነው።

3 የዚ​ህም ፍጻ​ሜው ትልና ጥፋት ነው። ደፋር ሰው​ነት ከመ​ከራ አት​ጠ​በ​ቅም።

4 ፈጥኖ የሚ​ያ​ምን ልቡ​ናው ቀሊል ነው፥ ኀጢ​አ​ትን የሚ​ሠ​ራም ራሱን ይበ​ድ​ላል።

5 ልቡ​ና​ውን ደስ የሚ​ያ​ሰኝ ሰው ይደ​ነ​ቃል።

6 ብዙ መና​ገ​ር​ንም የሚ​ጠላ ኀጢ​አ​ቱን ያሳ​ን​ሣል።

7 የሰ​ማ​ኸ​ውን ቃል አታ​ውጣ፥ አት​ድ​ገ​መ​ውም፥ ለዘ​ለ​ዓ​ለ​ሙም የባሰ አያ​ገ​ኝ​ህም።

8 በወ​ዳ​ጅና በጠ​ላት ዘንድ የም​ት​ና​ገ​ረው ነገር አይ​ኑር፥ ስተህ የሠ​ራ​ኸው ኀጢ​አ​ት​ህ​ንም አት​ና​ገር።

9 ቢሰማ አይ​ሰ​ው​ር​ል​ህ​ምና፥ እስ​ክ​ት​ሞ​ትም ድረስ ይጠ​ብ​ቅ​ሃል።

10 የሰ​ማ​ኸ​ውን ቃል አታ​ውጣ፥ ከዚ​ህም በኋላ የሚ​ያ​ገ​ኝህ ክፉ ነገር እን​ደ​ሌለ እመን።

11 አላ​ዋቂ ሰው የሰ​ማ​ውን ነገር እስ​ከ​ሚ​ያ​ወጣ ድረስ ይቅ​በ​ዘ​በ​ዛል፥ ልጅ የም​ት​ወ​ልድ ሴትም በምጥ እን​ደ​ም​ት​ጨ​ነቅ ይጨ​ነ​ቃል።

12 የተ​ወጋ ሰውም ጦሩን ከላዩ ይነ​ቅል ዘንድ እን​ደ​ሚ​ቸ​ኩል፥ አላ​ዋቂ ሰው የሰ​ማ​ውን ቃል ያወጣ ዘንድ ይቸ​ኩ​ላል።

13 ወዳ​ጅ​ህን አላ​ደ​ረገ እንደ ሆነ ወይም አድ​ርጎ እንደ ሆነ እን​ዳ​ይ​ደ​ግም ገሥ​ጸው።

14 ወዳ​ጅ​ህን፥ አል​ተ​ና​ገረ እንደ ሆነ ወይም ተና​ግሮ እንደ ሆነ እን​ዳ​ይ​ደ​ግም ገሥ​ጸው።

15 ወዳ​ጅ​ህን በጥ​ላቻ ነገር ተሠ​ር​ቶ​በት ይሆ​ና​ልና ገሥ​ጸው፤ ከልቡ ሳይ​ፈ​ቅድ የሚ​ሳ​ሳት ሰው አለና የነ​ገ​ሩ​ህን ነገር ሁሉ አት​መን።

16 በአ​ን​ደ​በቱ የማ​ይ​ሳ​ሳት ማን ነው?

17 ቍጣ ሳይ​በዛ ወዳ​ጅ​ህን ገሥ​ጸው፥ ስለ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሕግም ቍጣን አሳ​ል​ፋት።

18 ጥበብ ሁላ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን መፍ​ራት ናትና፥ ጥበ​ብም ሁላ ሕጉን ታስ​ጠ​ብ​ቃ​ለ​ችና።


እው​ነ​ተ​ኛና ሐሰ​ተኛ ጥበብ

19 ክፉን የሚ​ያ​ስ​ተ​ምር ጥበብ የለም፥ ለኃ​ጥ​ኣ​ንም ምክር ጥበብ የላ​ትም።

20 ከሁሉ የም​ት​ረ​ክስ ክፋት አለች፥ አእ​ምሮ የጐ​ደ​ለው አላ​ዋ​ቂም አለ።

21 ነገር ግን ከሚ​ራ​ቀቅ፥ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ሕግ ከሚ​ክድ ይልቅ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የሚ​ፈራ አላ​ዋቂ ይሻ​ላል።

22 እየ​በ​ደለ የሚ​ራ​ቀ​ቅና የሚ​ጠ​ነ​ቀቅ አለ፥ ለባ​ል​ን​ጀ​ራው የሚ​ያ​ደላ፥ ለወ​ዳ​ጁም ፍር​ድን የሚ​ያ​ቀና መስሎ ፍር​ድን የሚ​ለ​ውጥ ሰው አለ።

23 እያ​መ​ሰ​ገነ ለክፉ ነገር የሚ​ያ​ደላ ሰው አለ፥ ልቡ​ናው ግን ሽን​ገ​ላን ተሞ​ል​ት​ዋል።

24 በል​ቡ​ናው ሌላ ነገር እያለ ፊት አይቶ የሚ​ያ​ዳላ አለ፥ ባላ​ሰ​ብ​ኸ​ውም ነገር ይመ​ጣ​ብ​ሃል።

25 ኀይሉ ቢደ​ክም፥ በአ​ን​ተም ላይ ክፉ ማድ​ረግ ቢሳ​ነው፥ ያስ​ትህ ዘንድ መከ​ራን በግድ ያመ​ጣ​ብ​ሃል።

26 ሰው በመ​ልኩ ይታ​ወ​ቃ​ልና፥ ጠቢ​ብም በገጹ ይታ​ወ​ቃል።

27 ካለ​ባ​በ​ሱና ካካ​ሄዱ፥ ከአ​ሳ​ሣ​ቁም የተ​ነሣ፥ የሰው ጠባዩ ይታ​ወ​ቃል።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች