Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ

- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽሐፈ ሲራክ 18 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 ለዘ​ለ​ዓ​ለም ሕያው የሆነ እርሱ ሁሉን በአ​ን​ድ​ነት ፈጠረ።

2 እው​ነ​ተኛ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ብቻ ነው።

3 ሥራ​ውን ያውቅ ዘንድ ማን​ንም አላ​ሰ​ና​በ​ተ​ውም፤ የገ​ና​ና​ነ​ቱ​ንስ ፍለጋ ማን መር​ምሮ ያው​ቃል?

4 ከሀ​ሊ​ነ​ቱ​ንስ ማን መር​ምሮ ያው​ቃል? ቸር​ነ​ቱ​ንስ ማን ጠን​ቅቆ ይና​ገ​ራል?

5 መጨ​መ​ርም የለም፤ መቀ​ነ​ስም የለም፤ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የጌ​ት​ነ​ቱን ፍለጋ የሚ​ያ​ገኝ የለም።

6 ሰውን በፈ​ጠ​ረው ጊዜ ያን​ጊዜ ያዝ​ዘ​ዋል፤ ዘመ​ኑ​ንም ባስ​ጨ​ረ​ሰው ጊዜ ያን​ጊዜ ያሳ​ር​ፈ​ዋል።

7 ሰው ምን​ድን ነው? ጥቅ​ሙስ ምን​ድን ነው?

8 በጎ​ነቱ ምን​ድን ነው? ክፋ​ቱስ ምን​ድን ነው? የዘ​መ​ኑም ቍጥር ቢበዛ መቶ ዓመት ነው፤

9 በባ​ሕር ውስጥ እንደ አን​ዲት የውኃ ጠብታ፥ ከአ​ሸ​ዋ​ውም ሁሉ እንደ አን​ዲት የአ​ሸዋ ቅን​ጣት፥ እን​ዲሁ በዘ​ለ​ዓ​ለ​ማ​ዊ​ነት ዓመ​ታት ዘንድ የሰው ዘመኑ ጥቂት ነው።

10 ስለ​ዚህ ነገር እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይታ​ገ​ሣ​ቸ​ዋል። ምሕ​ረ​ቱን አሳ​ደ​ረ​ባ​ቸው።

11 ፍጻ​ሜ​ያ​ቸው ክፉ እንደ ሆነ አይቶ ዐወ​ቃ​ቸው፤ ምሕ​ረ​ቱን እን​ዲሁ አብ​ዝ​ት​ዋ​ልና።

12 ሰው ባል​ን​ጀ​ራ​ውን ብቻ ይቅር ይላል፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ግን ፍጥ​ረ​ቱን ሁሉ ይቅር ይላል፤

13 ይቈ​ጣል፥ ይገ​ር​ፋል፥ ይቅር ይላል፥ እረ​ኛም መን​ጋ​ውን እን​ዲ​መ​ልስ ይመ​ል​ሳል። በተ​ግ​ሣጹ የሚ​ታ​ገ​ሡ​ትን፥ ሕጉ​ንም የሚ​ከ​ተ​ሉ​ትን ሰዎች ይቅር ይላ​ቸ​ዋል።


የተ​ወ​ደደ ምጽ​ዋት

14 ልጄ ሆይ፥ በደ​ስ​ታህ መካ​ከል ኀዘ​ንን አታ​ስ​ገባ፤ በም​ት​ስ​ጠ​ውም ሁሉ ክፉ ነገ​ርን አት​ና​ገር።

15 ዝናም ዋዕ​ይን የሚ​ያ​ቀ​ዘ​ቅ​ዘው አይ​ደ​ለ​ምን? እን​ዲሁ በጎ ቃል ከመ​ስ​ጠት ይሻ​ላል።

16 እነሆ እን​ግ​ዲህ ከመ​ስ​ጠት መል​ካም ቃል አይ​ሻ​ል​ምን? ሁለ​ቱም ሁሉ በጻ​ድቅ ሰው ዘንድ ይገ​ኛሉ።

17 ንፉግ ልቡ​ና​ውን ደስ ሳይ​ለው ይሰ​ጣል። ሰነ​ፍም ይላ​ገ​ዳል አያ​መ​ሰ​ግ​ን​ምም።

18 ሳት​ና​ገር ተረዳ፥ ሳት​ታ​መ​ምም ዳን።

19 ሳይ​ፈ​ረ​ድ​ብህ ራስ​ህን መር​ምር፤ በመ​ከ​ራ​ህም ጊዜ ይቅ​ር​ታን ታገ​ኛ​ለህ።

20 ሳት​ደ​ክም ራስ​ህን አዋ​ርድ፥ በበ​ደ​ል​ህም ጊዜ ንስሓ ግባ።

21 ስእ​ለ​ት​ህን ፈጥ​ነህ ስጥ፤ ሳት​ሞ​ትም ጽድ​ቅን ሥራት።

22 ሳት​ሳ​ልም አስ​ቀ​ድ​መህ ስእ​ለ​ት​ህን አዘ​ጋጅ፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን እን​ደ​ሚ​ፈ​ታ​ተ​ነው ሰው አት​ሁን።

23 በተ​ቈ​ጣ​ህም ጊዜ የሞ​ትን ቀን ዐስብ፤ የፍ​ዳ​ህ​ንም ቀን ዐስብ፤ ንስ​ሓም ግባ ጸል​ይም።

24 በጥ​ጋ​ብህ ወራት የረ​ኃ​ብን ወራት ዐስብ። በተ​ድ​ላ​ህም ወራት የች​ግ​ርን ወራት ዐስብ።

25 ኑሮ ከጧት እስከ ማታ ድረስ ትለ​ዋ​ወ​ጣ​ለ​ችና፥ ሁሉም በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ዘንድ አንድ ጊዜ ፈጥኖ ይደ​ረ​ጋ​ልና።

26 ብልህ ሰው ግን ፈርቶ በሁሉ ይጠ​በ​ቃል፤ ኀጢ​አት በሚ​ሠ​ራ​በ​ትም ጊዜ ንስሓ ይገ​ባል።

27 አስ​ተ​ዋይ ሰው ሁሉ ጥበ​ብን ያገ​ኛ​ታል፤ ያገ​ኛ​ት​ንም ሰው ታስ​መ​ሰ​ግ​ነ​ዋ​ለች፥ ታስ​ከ​ብ​ረ​ዋ​ለ​ችም፥

28 ነገር ዐዋ​ቂ​ዎች ራሳ​ቸው በል​ቡ​ና​ቸው ይራ​ቀ​ቃሉ፤ የተ​ረዳ ምሳ​ሌ​ንም ይና​ገ​ራሉ።

29 አት​ሂድ፥ የኀ​ጢ​አ​ት​ንም ፈቃድ አት​ከ​ተል፤ ከክፉ ፍት​ወ​ትም ራቅ።

30 ለሰ​ው​ነ​ትህ የም​ት​ወ​ድ​ደ​ውን ከሰ​ጠ​ኻት፥ ጠላ​ት​ህን በአ​ንተ የጨ​ከነ ታደ​ር​ገ​ዋ​ለች።

31 በተ​ድላ ብዛት ደስ አይ​በ​ልህ፤ ከእ​ር​ስ​ዋም ጋር ደስ ይልህ ዘንድ አት​ለ​ምን።

32 እን​ዳ​ት​ያዝ አንተ ድሃ ሳለህ፥ በከ​ረ​ጢ​ት​ህም ምንም ሳይ​ኖ​ርህ አት​በ​ደር።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች